ራእይ 4 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ራእይ 4:1-11

በሰማይ ያለው ዙፋን

1ከዚህ በኋላ እነሆ፤ በሰማይ የተከፈተ በር አየሁ፤ ቀደም ሲል እንደ መለከት ሲናገረኝ የሰማሁት ድምፅ፣ “ወደዚህ ና፤ ከዚህም በኋላ ሊሆን የሚገባውን ነገር አሳይሃለሁ” አለኝ። 2እኔም ወዲያወኑ በመንፈስ ነበርሁ፤ እነሆም በሰማይ ዙፋን ቆሟል፤ በዙፋኑም ላይ የተቀመጠ ነበረ። 3ተቀምጦም የነበረው የኢያስጲድንና የሰርዲኖን ዕንይመስል ነበር። የመረግድ ዕንየመሰለ ቀስተ ደመናም ዙፋኑን ከብቦት ነበር። 4በዙፋኑ ዙሪያ ሌሎች ሃያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፤ በእነርሱም ላይ ነጭ ልብስ የለበሱና በራሳቸውም ላይ የወርቅ አክሊል የደፉ ሃያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር። 5ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ፣ ነጐድጓድም ወጣ፤ በዙፋኑ ፊት ሰባት መብራቶች ይበሩ ነበር፤ እነዚህም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት4፥5 ወይም ሰባት ዕጥፍ መንፈስ ናቸው። 6ደግሞም በዙፋኑ ፊት እንደ መስተዋት የጠራ የብርጭቆ ባሕር ነበረ።

በዙፋኑ መካከል፣ በዙሪያውም ከፊትና ከኋላ በዐይን የተሞሉ አራት ሕያዋን ፍጡራን ነበሩ። 7የመጀመሪያው ሕያው ፍጡር አንበሳ፣ ሁለተኛው በሬ ይመስሉ ነበር፤ ሦስተኛው የሰው ፊት የሚመስል ፊት ነበረው፤ አራተኛው ደግሞ የሚበርር ንስር ይመስል ነበር። 8አራቱም ሕያዋን ፍጡራን እያንዳንዳቸው ስድስት ስድስት ክንፎች ነበሯቸው፤ በዙሪያቸውና በውስጣቸው በዐይኖች የተሞሉ ነበሩ፤ ቀንና ሌሊትም፦

“ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣

የነበረው፣ ያለውና የሚመጣው፤

ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ”

ማለትን አያቋርጡም። 9ሕያዋን ፍጡራኑ በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠውና ከዘላለም እስከ ዘላለም ሕያው ሆኖ ለሚኖረው ክብር፣ ሞገስና ምስጋና በሚሰጡበት ጊዜ፣ 10ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋኑ ላይ በተቀመጠው ፊት ተደፍተው፣ ከዘላለም እስከ ዘላለም ሕያው ሆኖ ለሚኖረው ይሰግዱ ነበር፤ አክሊላቸውንም በዙፋኑ ፊት አስቀምጠው እንዲህ ይላሉ፤

11“ጌታችንና አምላካችን ሆይ፤

ክብርና ሞገስ፣ ኀይልም ልትቀበል ይገባሃል፤

አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና፤

በፈቃድህም ተፈጥረዋልና፤

ሆነዋልምና።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

啟示錄 4:1-11

天上的敬拜

1此後,我再觀看,見天上有一扇門開了,又聽見剛才那個像號角般響亮的聲音對我說:「你上這裡來,我要把以後必發生的事指示給你看。」 2我便立刻被聖靈感動,看見天上安設著一個寶座,有一位坐在寶座上, 3閃耀著碧玉和紅寶石般的光彩。有一道翡翠般的彩虹圍繞著寶座。 4寶座的周圍設有二十四個座位,有二十四位長老坐在上面,他們身穿白袍,頭戴金冠。 5從寶座中有閃電、響聲、雷鳴發出,寶座前面燃燒著七把火炬,代表4·5 代表」希臘文是「就是」。上帝的七靈。 6寶座前還有一個水晶般的玻璃海,寶座的四周有四個活物,他們前後都長滿了眼睛。 7第一個活物像獅子,第二個像牛犢,第三個有人的面孔,第四個像飛鷹。 8這四個活物各有三對翅膀,翅膀內外都長滿眼睛。他們晝夜不停地說:

「聖哉!聖哉!聖哉!

主上帝是昔在、今在、

以後永在的全能者。」

9每逢這些活物將榮耀、尊貴、感謝獻給坐在寶座上、活到永永遠遠的那位時, 10二十四位長老就俯伏在坐寶座的那位面前,敬拜那位永活者,又摘下他們頭上的冠冕,放在寶座前,說:

11「我們的主,我們的上帝,

你配得榮耀、尊貴和權能,

因你創造了萬物,

萬物都因你的旨意被創造而存在。」