ራእይ 16 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ራእይ 16:1-21

ሰባቱ የእግዚአብሔር ቍጣ ጽዋዎች

1ከዚያም ለሰባቱ መላእክት፣ “ሂዱ፤ ሰባቱን የእግዚአብሔር ቍጣ ጽዋዎች በምድር ላይ አፍስሱ” የሚል ታላቅ ድምፅ ከቤተ መቅደሱ ሰማሁ።

2የመጀመሪያው መልአክ ሄዶ ጽዋውን በምድር ላይ አፈሰሰ፤ የአውሬውን ምልክት በተቀበሉትና ለምስሉም በሰገዱት ሰዎች ላይ ክፉኛ የሚያሠቃይ ቍስል ወጣባቸው።

3ሁለተኛው መልአክ ጽዋውን በባሕር ላይ አፈሰሰ፤ ባሕሩም እንደ ሞተ ሰው ደም ሆነ፤ በባሕሩ ውስጥ የሚኖሩ ሕይወት ያላቸው ነገሮች ሁሉ ሞቱ።

4ሦስተኛው መልአክ ጽዋውን በወንዞችና በውሃ ምንጮች ላይ አፈሰሰ፤ እነርሱም ደም ሆኑ። 5ከዚያም በውሆች ላይ ሥልጣን ያለው መልአክ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ያለህና የነበርህ ቅዱሱ ሆይ፤

እንዲህ ስለ ፈረድህ፣

አንተ ጻድቅ ነህ፤

6የቅዱሳንንና የነቢያትን ደም ስላፈሰሱ፣

አንተም ደግሞ ደም እንዲጠጡ አደረግሃቸው፤ ይህ የሚገባቸው ነውና።”

7እንዲሁም ከመሠዊያው እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፤

“አዎን፤ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ ሆይ፤

ፍርድህ እውነትና ጽድቅ ነው።”

8አራተኛውም መልአክ ጽዋውን በፀሓይ ላይ አፈሰሰ፤ ፀሓይም ሰዎችን በእሳት እንድታቃጥል ኀይል ተሰጣት። 9እነርሱም በታላቅ ሐሩር ተቃጠሉ፤ በእነዚህም መቅሠፍቶች ላይ ሥልጣን ያለውን የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ እንጂ ንስሓ አልገቡም፤ ክብርም አልሰጡትም።

10አምስተኛውም መልአክ ጽዋውን በአውሬው ዙፋን ላይ አፈሰሰ፤ የአውሬውም መንግሥት በጨለማ ተዋጠ፤ ሰዎችም ከሥቃያቸው የተነሣ ምላሳቸውን ያኝኩ ነበር፤ 11ደግሞም ከሥቃያቸውና ከቍስላቸው የተነሣ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ እንጂ ከሥራቸው ንስሓ አልገቡም።

12ስድስተኛውም መልአክ ጽዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከምሥራቅ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲዘጋጅላቸው የወንዙ ውሃ ደረቀ። 13ከዚያም ከዘንዶው አፍ፣ ከአውሬው አፍና ከሐሰተኛው ነቢይ አፍ እንቍራሪት የሚመስሉ ሦስት ርኩሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ። 14እነርሱም ምልክቶች የሚያደርጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸው፤ ሁሉን በሚችል አምላክ ታላቅ ቀን ለሚሆነው ጦርነት እንዲሰበስቧቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይሄዳሉ።

15“እነሆ፤ እንደ ሌባ እመጣለሁ፤ ዕራቍቱን እንዳይሆን ኀፍረቱም እንዳይታይ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ሰው ብፁዕ ነው።”

16እነርሱም ነገሥታቱን በዕብራይስጥ አርማጌዶን በሚባል ስፍራ ሰበሰቧቸው።

17ሰባተኛውም መልአክ ጽዋውን በአየር ላይ አፈሰሰ፤ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ካለው ዙፋንም “ተፈጸመ!” የሚል ታላቅ ድምፅ ወጣ። 18ከዚያም መብረቅ፣ ድምፅ፣ ነጐድጓድና ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ላይ ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ የምድር መናወጥ ታይቶ አይታወቅም፤ ነውጡም እጅግ ታላቅ ነበር። 19ታላቂቱ ከተማ ከሦስት ተከፈለች፤ የሕዝቦች ከተሞችም ፈራረሱ፤ እግዚአብሔርም ታላቂቱን ባቢሎን አስታወሰ፤ በብርቱ ቍጣው ወይን ጠጅ የተሞላውን ጽዋ ሰጣት። 20ደሴቶች ሁሉ ሸሹ፤ ተራሮችም ሊገኙ አልቻሉም። 21በሚዛን ሲመዘን እያንዳንዱ አርባ አምስት ኪሎ ግራም16፥21 ግሪኩ አንድ ታላንት ይለዋል። የሚሆን ታላቅ በረዶ በሰዎች ላይ ከሰማይ ወረደባቸው፤ መቅሠፍቱ እጅግ አሠቃቂ ስለ ነበር፣ ሰዎቹ ከበረዶው መቅሠፍት የተነሣ እግዚአብሔርን ተሳደቡ።

New International Reader’s Version

Revelation 16:1-21

The Seven Bowls of God’s Great Anger

1Then I heard a loud voice from the temple speaking to the seven angels. “Go,” it said. “Pour out the seven bowls of God’s great anger on the earth.”

2The first angel went and poured out his bowl on the land. Ugly and painful sores broke out on people. Those people had the mark of the beast and worshiped its statue.

3The second angel poured out his bowl on the sea. It turned into blood like the blood of a dead person. Every living thing in the sea died.

4The third angel poured out his bowl on the rivers and springs of water. They became blood. 5Then I heard the angel who was in charge of the waters. He said,

“Holy One, the way you judge is fair.

You are the God who is and who was.

6Those who worship the beast have poured out blood.

They have poured out the life’s blood of your holy people and your prophets.

So you have given blood to drink to those who worship the beast.

That’s exactly what they should get.”

7Then I heard the altar reply. It said,

“Lord God who rules over all,

the way you judge is true and fair.”

8The fourth angel poured out his bowl on the sun. The sun was allowed to burn people with fire. 9They were burned by the blazing heat. So they spoke evil things against the name of God, who controlled these plagues. But they refused to turn away from their sins. They did not give glory to God.

10The fifth angel poured out his bowl on the throne of the beast. The kingdom of the beast became very dark. People chewed on their tongues because they were suffering so much. 11They spoke evil things against the God of heaven. They did this because of their pains and their sores. But they refused to turn away from the sins they had committed.

12The sixth angel poured out his bowl on the great river Euphrates. Its water dried up to prepare the way for the kings from the East. 13Then I saw three evil spirits that looked like frogs. They came out of the mouths of the dragon, the beast and the false prophet. 14They are spirits of demons that perform signs. They go out to gather the kings of the whole world for battle. This battle will take place on the great day of the God who rules over all.

15“Look! I am coming like a thief! Blessed is anyone who stays awake and keeps their clothes on. Then they will be ready. They will not be caught naked and so be put to shame.”

16Then the evil spirits gathered the kings together. In the Hebrew language, the place where the kings met is called Armageddon.

17The seventh angel poured out his bowl into the air. Out of the temple came a loud voice from the throne. It said, “It is done!” 18Then there came flashes of lightning, rumblings, thunder and a powerful earthquake. There has never been an earthquake as terrible as this. One like this hasn’t happened while human beings have lived on earth. 19The great city split into three parts. The cities of the nations crumbled and fell. God remembered Babylon the Great. He gave Babylon the cup filled with the wine of his terrible anger. 20Every island ran away. The mountains could not be found. 21Huge hailstones weighing about 100 pounds each fell from the sky. The hail crushed people. And they spoke evil things against God because of the plague. That’s because the plague of hail was so terrible.