ራእይ 15 – NASV & BDS

New Amharic Standard Version

ራእይ 15:1-8

ሰባቱ መላእክትና ሰባቱ መቅሠፍቶች

1ሌላም ታላቅና አስደናቂ ምልክት በሰማይ አየሁ፤ የመጨረሻዎቹን ሰባት መቅሠፍቶች የያዙ ሰባት መላእክት አየሁ፤ የመጨረሻ የተባሉትም የእግዚአብሔር ቍጣ የሚፈጸመው በእነርሱ በመሆኑ ነው። 2ከእሳት ጋር የተቀላቀለ የብርጭቆ ባሕር የሚመስል አየሁ፤ በባሕሩም አጠገብ አውሬውን፣ ምስሉንና የስሙን ቍጥር ድል የነሡትን ቆመው አየሁ፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን በገና ይዘው፣ 3የእግዚአብሔር ባሪያ የሆነውን የሙሴን መዝሙርና የበጉን መዝሙር እንዲህ እያሉ ይዘምሩ ነበር፤

“ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ ሆይ፤

ሥራህ ታላቅና አስደናቂ ነው።

የዘመናት15፥3 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ሕዝቦች ይላሉ። ንጉሥ ሆይ፤

መንገድህ ጽድቅና እውነት ነው።

4ጌታ ሆይ፤ አንተን የማይፈራ፣

ስምህን የማያከብርስ ማን ነው?

አንተ ብቻ ቅዱስ ነህና።

የጽድቅ ሥራህ ስለ ተገለጠ፣

ሕዝቦች ሁሉ ይመጣሉ፤

በፊትህም ይሰግዳሉ።”

5ከዚህ በኋላም አየሁ፤ በሰማይ ያለው ቤተ መቅደስ፣ ይኸውም የምስክሩ ድንኳን ተከፍቶ ነበር። 6ሰባቱን መቅሠፍቶች የያዙት ሰባቱ መላእክት ከቤተ መቅደሱ ወጡ፤ እነርሱም ከተልባ እግር የተሠራ ንጹሕ የሚያበራ ልብስ ለብሰው፣ ደረታቸውንም በወርቅ መታጠቂያ ታጥቀው ነበር። 7ከዚያም ከአራቱ ሕያዋን ፍጡራን አንዱ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው አምላክ ቍጣ የተሞሉትን ሰባት የወርቅ ጽዋዎች ለሰባቱ መላእክት ሰጣቸው። 8ቤተ መቅደሱም ከእግዚአብሔር ክብር፣ ከኀይሉም በወጣው ጢስ ተሞላ፤ የሰባቱ መላእክት ሰባት መቅሠፍቶች እስኪፈጸሙ ድረስ ማንም ወደ ቤተ መቅደሱ መግባት አልቻለም።

La Bible du Semeur

Apocalypse 15:1-8

Le signe des sept derniers fléaux

1Puis je vis dans le ciel un autre signe grandiose qui me remplit d’étonnement : sept anges portant sept fléaux, les sept derniers par lesquels se manifeste la colère de Dieu. 2Je vis aussi comme une mer cristalline mêlée de feu. Ceux qui avaient vaincu la bête, son image et le nombre de son nom se tenaient sur la mer de cristal. S’accompagnant de harpes divines, 3ils chantaient le cantique de Moïse15.3 Voir Ex 15., le serviteur de Dieu, et le cantique de l’Agneau. Ils chantaient :

Seigneur, Dieu, Tout-Puissant,

tes œuvres sont grandes et admirables.

Roi de tous les peuples,

ce que tu fais est juste

et conforme à la vérité !

4Qui oserait, Seigneur,

refuser de te craindre

et de te rendre gloire ?

Car toi seul tu es saint ;

tous les peuples viendront

pour se prosterner devant toi,

car il deviendra manifeste

que tes actions sont justes.

Les sept coupes de la colère de Dieu15.5 Voir Es 6.4.

5Après cela je vis s’ouvrir dans le ciel le Temple qui abritait le tabernacle du témoignage.

6Les sept anges porteurs des sept fléaux sortirent du Temple. Ils étaient vêtus de tuniques d’un lin pur, éclatant, et leur taille était serrée par une ceinture d’or.

7L’un des quatre êtres vivants remit aux sept anges sept coupes d’or remplies de la colère du Dieu qui vit éternellement. 8Alors la gloire et la puissance de Dieu remplirent le Temple de fumée15.8 Comparer Ap 8 et 9. Les fléaux rappellent les plaies d’Egypte., en sorte que personne ne put y pénétrer tant que les sept fléaux, déclenchés par les sept anges, ne s’étaient pas accomplis.