ራእይ 10 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ራእይ 10:1-11

መልአኩና ትንሿ መጽሐፍ

1ከዚህ በኋላ ሌላ ብርቱ መልአክ ደመና ተጐናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ እርሱም በራሱ ላይ ቀስተ ደመና ነበር። ፊቱ እንደ ፀሓይ፣ እግሮቹ እንደ እሳት ዐምዶች ነበሩ። 2በእጁም የተከፈተች ትንሽ ጥቅልል መጽሐፍ ይዞ ነበር፤ ቀኝ እግሩን በባሕር ላይ፣ ግራ እግሩን በምድር ላይ አኖረ፤ 3እንደሚያገሣ አንበሳም ድምፁን ከፍ አድርጎ ጮኸ፤ በጮኸም ጊዜ የሰባቱ ነጐድጓዶች ድምፆች ተናገሩ። 4ሰባቱ ነጐድጓዶች በተናገሩ ጊዜ፣ ለመጻፍ ተዘጋጀሁ፤ ነገር ግን፣ “ሰባቱ ነጐድጓዶች የተናገሩትን በማኅተም ዝጋው እንጂ አትጻፍ” የሚል ድምፅ ከሰማይ ሰማሁ።

5ከዚህ በኋላ በባሕርና በምድር ላይ ቆሞ ያየሁት መልአክ ቀኝ እጁን ወደ ሰማይ አነሣ፤ 6እርሱም ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው፣ ሰማይንና በውስጡ ያሉትን፣ ምድርንና በውስጧ ያሉትን፣ ባሕርንና በውስጡ ያሉትን በፈጠረው በእርሱ ማለ፤ እንዲህም አለ፤ “ከእንግዲህ መዘግየት አይኖርም፤ 7ነገር ግን ሰባተኛው መልአክ መለከቱን በሚነፋባቸው ቀኖች፣ ለአገልጋዮቹ ለነቢያት በገለጠላቸው መሠረት የእግዚአብሔር ምስጢር ይፈጸማል።”

8ከዚያም ከሰማይ የሰማሁት ድምፅ እንደ ገና እንዲህ ሲል ተናገረ፤ “ሂድ፤ በባሕርና በምድር ላይ ከቆመው መልአክ እጅ የተከፈተችውን ጥቅልል መጽሐፍ ውሰድ።”

9እኔም ወደ መልአኩ ሄጄ ትንሿን ጥቅልል መጽሐፍ እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፤ እርሱም፣ “ውሰድና ብላት፤ ሆድህን መራራ ታደርገዋለች፤ በአፍህ ግን እንደ ማር ትጣፍጣለች” አለኝ። 10ትንሿንም መጽሐፍ ከመልአኩ እጅ ተቀብዬ በላኋት፤ በአፌ እንደ ማር ጣፈጠች፤ ከበላኋት በኋላ ግን ሆዴ መራራ ሆነ፤ 11ከዚያም፣ “ስለ ብዙ ሕዝቦች፣ ወገኖች፣ ቋንቋዎችና ነገሥታት እንደ ገና ትንቢት ልትናገር ይገባሃል” ተባልሁ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

启示录 10:1-11

天使与小书卷

1我看见另一位大力天使从天而降。他身披云霞,头顶彩虹,脸如太阳,双腿如火柱, 2手中拿着一卷打开了的小书卷,右脚踏在海中,左脚踏在地上。 3他大喊的时候,声如狮吼,之后有七声雷鸣。 4我正要将雷鸣的意思记录下来,就听见天上有声音说:“你要封住七声雷鸣所说的事,别写下来。”

5我刚才所见的那位脚踏海洋和陆地的天使向天举起右手, 6凭着活到永永远远、创造天地海洋和其中一切的上帝起誓说:“必不再耽延了。 7等第七位天使吹响号角时,上帝奥秘的计划就实现了,正如上帝向祂的奴仆——众先知所宣告的。”

8先前从天上对我说话的声音又吩咐我:“你去,从那位脚踏海洋陆地的天使手中把展开的小书卷拿来。”

9于是,我走到那天使面前,请他将小书卷给我。他对我说:“拿去,把它吃了。你的腹中会感到苦涩,可是你口中会觉得甘甜如蜜。” 10我就从天使手中接过小书卷,将它吃了,我口中果然甘甜如蜜,之后腹中觉得苦涩。 11那天使又对我说:“你必要再对许多民族、国家、语言族群、君王说预言。”