ምሳሌ 5 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 5:1-23

ከአመንዝራነት መጠንቀቅ

1ልጄ ሆይ፤ ጥበቤን ልብ በል፤

የማስተዋል ቃሌንም በጥሞና አድምጥ፤

2ይህም ልባምነትን ገንዘብ እንድታደርግ፣

ከንፈሮችህም ዕውቀትን እንዲጠብቁ ነው።

3የአመንዝራ ሴት ከንፈር ማር ያንጠባጥባልና፤

አንደበቷም ከቅቤ ይለሰልሳል፤

4በመጨረሻ ግን እንደ እሬት ትመርራለች፤

ሁለት አፍ እንዳለውም ስል ሰይፍ ትሆናለች።

5እግሮቿ ወደ ሞት ይወርዳሉ፤

ርምጃዎቿም በቀጥታ ወደ ሲኦል5፥5 ወይም መቃብር ያመራሉ።

6ስለ ሕይወት መንገድ ደንታ የላትም፤

መንገዶቿ ዘወርዋራ ናቸው፤ ለእርሷ ግን አይታወቃትም።

7እንግዲህ፣ ልጆቼ ሆይ፤ አድምጡኝ፤

ከምነግራችሁ ቃል ፈቀቅ አትበሉ።

8መንገድህን ከእርሷ አርቅ፤

በደጃፏም አትለፍ፤

9ይኸውም ጕብዝናህን ለሌሎች፣

ዕድሜህንም ለጨካኞች እንዳትሰጥ ነው፤

10ባዕዳን በሀብትህ እንዳይፈነጥዙ፣

ልፋትህም የሌላውን ሰው ቤት እንዳያበለጽግ ነው።

11በዕድሜህ መጨረሻ ታቃሥታለህ፤

ሥጋህና ሰውነትህ ሲከዳህ።

12እንዲህም ትላለህ፤ “ምነው ተግሣጽን ጠላሁ!

ልቤስ ምነው መታረምን ናቀ!

13የመምህሮቼን ቃል አልሰማሁም፤

አሠልጣኞቼንም አላደመጥኋቸውም፤

14በመላው ጉባኤ ፊት፣

ወደ ፍጹም ጥፋት ተቃርቤአለሁ።”

15ከገዛ ማጠራቀሚያህ ውሃ፣

ከገዛ ጕድጓድህም የሚፈልቀውን ውሃ ጠጣ።

16ምንጮችህ ተርፈው ወደ ሜዳ፣

ወንዞችህስ ወደ አደባባይ ሊፈስሱ ይገባልን?

17ለአንተ ብቻ ይሁኑ፤

ባዕዳን አይጋሩህ።

18ምንጭህ ቡሩክ ይሁን፤

በልጅነት ሚስትህም ደስ ይበልህ።

19እርሷ እንደ ተወደደች ዋላ፣ እንደ ተዋበች ሚዳቋ ናት፤

ጡቶቿ ዘወትር ያርኩህ፤

ፍቅሯም ሁልጊዜ ይማርክህ።

20ልጄ ሆይ፤ በአመንዝራ ሴት ፍቅር ለምን ትሰክራለህ?

የሌላዪቱንስ ሴት ብብት ስለ ምን ታቅፋለህ?

21የሰው መንገድ በእግዚአብሔር ፊት ግልጥ ነውና፤

እርሱ መሄጃውን ሁሉ ይመረምራል።

22ክፉውን ሰው የገዛ መጥፎ ሥራው ያጠምደዋል፤

የኀጢአቱም ገመድ ጠፍሮ ይይዘዋል።

23ከተግሣጽ ጕድለት የተነሣ ይሞታል፤

ከተላላነቱም ብዛት መንገድ ይስታል።

New International Version – UK

Proverbs 5:1-23

Warning against adultery

1My son, pay attention to my wisdom,

turn your ear to my words of insight,

2that you may maintain discretion

and your lips may preserve knowledge.

3For the lips of the adulterous woman drip honey,

and her speech is smoother than oil;

4but in the end she is bitter as gall,

sharp as a double-edged sword.

5Her feet go down to death;

her steps lead straight to the grave.

6She gives no thought to the way of life;

her paths wander aimlessly, but she does not know it.

7Now then, my sons, listen to me;

do not turn aside from what I say.

8Keep to a path far from her,

do not go near the door of her house,

9lest you lose your honour to others

and your dignity5:9 Or years to one who is cruel,

10lest strangers feast on your wealth

and your toil enrich the house of another.

11At the end of your life you will groan,

when your flesh and body are spent.

12You will say, ‘How I hated discipline!

How my heart spurned correction!

13I would not obey my teachers

or turn my ear to my instructors.

14And I was soon in serious trouble

in the assembly of God’s people.’

15Drink water from your own cistern,

running water from your own well.

16Should your springs overflow in the streets,

your streams of water in the public squares?

17Let them be yours alone,

never to be shared with strangers.

18May your fountain be blessed,

and may you rejoice in the wife of your youth.

19A loving doe, a graceful deer –

may her breasts satisfy you always,

may you ever be intoxicated with her love.

20Why, my son, be intoxicated with another man’s wife?

Why embrace the bosom of a wayward woman?

21For your ways are in full view of the Lord,

and he examines all your paths.

22The evil deeds of the wicked ensnare them;

the cords of their sins hold them fast.

23For lack of discipline they will die,

led astray by their own great folly.