ምሳሌ 5 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 5:1-23

ከአመንዝራነት መጠንቀቅ

1ልጄ ሆይ፤ ጥበቤን ልብ በል፤

የማስተዋል ቃሌንም በጥሞና አድምጥ፤

2ይህም ልባምነትን ገንዘብ እንድታደርግ፣

ከንፈሮችህም ዕውቀትን እንዲጠብቁ ነው።

3የአመንዝራ ሴት ከንፈር ማር ያንጠባጥባልና፤

አንደበቷም ከቅቤ ይለሰልሳል፤

4በመጨረሻ ግን እንደ እሬት ትመርራለች፤

ሁለት አፍ እንዳለውም ስል ሰይፍ ትሆናለች።

5እግሮቿ ወደ ሞት ይወርዳሉ፤

ርምጃዎቿም በቀጥታ ወደ ሲኦል5፥5 ወይም መቃብር ያመራሉ።

6ስለ ሕይወት መንገድ ደንታ የላትም፤

መንገዶቿ ዘወርዋራ ናቸው፤ ለእርሷ ግን አይታወቃትም።

7እንግዲህ፣ ልጆቼ ሆይ፤ አድምጡኝ፤

ከምነግራችሁ ቃል ፈቀቅ አትበሉ።

8መንገድህን ከእርሷ አርቅ፤

በደጃፏም አትለፍ፤

9ይኸውም ጕብዝናህን ለሌሎች፣

ዕድሜህንም ለጨካኞች እንዳትሰጥ ነው፤

10ባዕዳን በሀብትህ እንዳይፈነጥዙ፣

ልፋትህም የሌላውን ሰው ቤት እንዳያበለጽግ ነው።

11በዕድሜህ መጨረሻ ታቃሥታለህ፤

ሥጋህና ሰውነትህ ሲከዳህ።

12እንዲህም ትላለህ፤ “ምነው ተግሣጽን ጠላሁ!

ልቤስ ምነው መታረምን ናቀ!

13የመምህሮቼን ቃል አልሰማሁም፤

አሠልጣኞቼንም አላደመጥኋቸውም፤

14በመላው ጉባኤ ፊት፣

ወደ ፍጹም ጥፋት ተቃርቤአለሁ።”

15ከገዛ ማጠራቀሚያህ ውሃ፣

ከገዛ ጕድጓድህም የሚፈልቀውን ውሃ ጠጣ።

16ምንጮችህ ተርፈው ወደ ሜዳ፣

ወንዞችህስ ወደ አደባባይ ሊፈስሱ ይገባልን?

17ለአንተ ብቻ ይሁኑ፤

ባዕዳን አይጋሩህ።

18ምንጭህ ቡሩክ ይሁን፤

በልጅነት ሚስትህም ደስ ይበልህ።

19እርሷ እንደ ተወደደች ዋላ፣ እንደ ተዋበች ሚዳቋ ናት፤

ጡቶቿ ዘወትር ያርኩህ፤

ፍቅሯም ሁልጊዜ ይማርክህ።

20ልጄ ሆይ፤ በአመንዝራ ሴት ፍቅር ለምን ትሰክራለህ?

የሌላዪቱንስ ሴት ብብት ስለ ምን ታቅፋለህ?

21የሰው መንገድ በእግዚአብሔር ፊት ግልጥ ነውና፤

እርሱ መሄጃውን ሁሉ ይመረምራል።

22ክፉውን ሰው የገዛ መጥፎ ሥራው ያጠምደዋል፤

የኀጢአቱም ገመድ ጠፍሮ ይይዘዋል።

23ከተግሣጽ ጕድለት የተነሣ ይሞታል፤

ከተላላነቱም ብዛት መንገድ ይስታል።

Ketab El Hayat

الأمثال 5:1-23

تحذير من الزنى

1يَا ابْنِي أَصْغِ إِلَى حِكْمَتِي، وَأَرْهِفْ أُذُنَكَ إِلَى قَوْلِ فِطْنَتِي. 2لِكَيْ تَدَّخِرَ الْفِطْنَةَ، وَتَرْعَى شَفَتَاكَ الْعِلْمَ. 3لأَنَّ شَفَتَيِ الْمَرْأَةِ الْعَاهِرَةِ تَقْطُرَانِ شَهْداً، وَحَدِيثَهَا أَكْثَرُ نُعُومَةً مِنَ الزَّيْتِ، 4لَكِنَّ عَاقِبَتَهَا مُرَّةٌ كَالْعَلْقَمِ، حَادَّةٌ كَسَيْفٍ ذِي حَدَّيْنِ. 5تَنْحَدِرُ قَدَمَاهَا إِلَى الْمَوْتِ، وَخَطْوَاتُهَا تَتَشَبَّثُ بِالْهَاوِيَةِ. 6لَا تَتَأَمَّلُ طَرِيقَ الْحَيَاةِ؛ تَتَرَنَّحُ خَطْوَاتُهَا وَهِيَ لَا تُدْرِكُ ذَلِكَ.

7وَالآنَ أَصْغُوا إِلَيَّ أَيُّهَا الْبَنُونَ، وَلا تَهْجُرُوا كَلِمَاتِ فَمِي. 8أَبْعِدْ طَرِيقَكَ عَنْهَا، وَلا تَقْتَرِبْ مِنْ بَابِ بَيْتِهَا، 9لِئَلّا تُعْطِيَ كَرَامَتَكَ لِلآخَرِينَ، وَسِنِي عُمْرِكَ لِمَنْ لَا يَرْحَمُ، 10فَيَسْتَهْلِكَ الْغُرَبَاءُ ثَرْوَتَكَ حَتَّى الشِّبَعِ، وَتَضْحَى غَلَّةُ أَتْعَابِكَ فِي بَيْتِ الأَجْنَبِيِّ. 11فَتَنُوحَ فِي أَوَاخِرِ حَيَاتِكَ، عِنْدَ فَنَاءِ لَحْمِكَ وَجَسَدِكَ، لإِصَابَتِكَ بِأَمْرَاضٍ مُعْدِيَةٍ، 12وَتَقُولَ: «كَيْفَ مَقَتُّ التَّأْدِيبَ، وَاسْتَخَفَّ قَلْبِي بِالتَّوْبِيخِ، 13فَلَمْ أَصْغِ إِلَى تَوْجِيهِ مُرْشِدِيَّ، وَلا اسْتَمَعْتُ إِلَى مُعَلِّمِيَّ. 14حَتَّى كِدْتُ أَتْلَفُ فِي وَسَطِ الْجُمْهُورِ وَالْجَمَاعَةِ».

15اشْرَبْ مَاءً مِنْ جُبِّكَ، وَمِيَاهاً جَارِيَةً مِنْ بِئْرِكَ. 16أَيَنْبَغِي عَلَى يَنَابِيعِكَ أَنْ تَفِيضَ إِلَى الْخَارِجِ كَأَنْهَارِ مِيَاهٍ فِي الشَّوَارِعِ؟ 17لِيَكُنْ أَوْلادُكَ لَكَ وَحْدَكَ، لَا نَصِيبَ لِلْغُرَبَاءِ مَعَكَ فِيهِمْ. 18لِيَكُنْ يَنْبُوعُ عِفَّتِكَ مُبَارَكاً، وَاغْتَبِطْ بِامْرَأَةِ شَبَابِكَ، 19فَتَكُونَ كَالظَّبْيَةِ الْمَحْبُوبَةِ وَالْوَعْلَةِ الْبَهِيَّةِ، فَتَرْتَوِيَ مِنْ فَيْضِ فِتْنَتِهَا، وَتَظَلَّ دَائِماً أَسِيرَ حُبِّهَا. 20لِمَاذَا تُوْلَعُ يَا ابْنِي بِالْمَرْأَةِ الْعَاهِرَةِ أَوْ تَحْتَضِنُ الْغَرِيبَةَ؟ 21فَإِنَّ تَصَرُّفَاتِ الإِنْسَانِ مَكْشُوفَةٌ أَمَامَ عَيْنَيِ الرَّبِّ، وَهُوَ يُبْصِرُ جَمِيعَ طُرُقِهِ. 22آثَامُ الْمُنَافِقِ تَتَصَيَّدُهُ، وَيَعْلَقُ بِحِبَالِ خَطِيئَتِهِ. 23يَمُوتُ افْتِقَاراً إِلَى التَّأْدِيبِ، وَبِحُمْقِهِ يَتَشَرَّدُ.