ምሳሌ 21 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 21:1-31

1የንጉሥ ልብ በእግዚአብሔር እጅ ነው፤

እርሱም እንደ ቦይ ውሃ ደስ ወዳሰኘው ይመራዋል።

2ለሰው መንገዱ ሁሉ ቀና ይመስለዋል፤

እግዚአብሔር ግን ልብን ይመዝናል።

3ከመሥዋዕት ይልቅ ጽድቅንና ፍትሕን ማድረግ፣

በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አለው።

4ትዕቢተኛ ዐይን፣ እብሪተኛ ልብ፣

የክፉዎችም መብራት ኀጢአት ናቸው።

5የትጉህ ሰው ዕቅድ ወደ ትርፍ ያመራል፤

ችኰላም ወደ ድኽነት ያደርሳል።

6በሐሰተኛ አንደበት የተገኘ ሀብት፣

በንኖ የሚጠፋ ተን፣ ለሞትም የሚያበቃ ወጥመድ ነው።21፥6 አንዳንድ የዕብራይስጥ ጽሑፎች፣ የሰብዓ ሊቃናትና የቩልጌት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አያሌ የዕብራይስጥ ጽሑፎች ግን ሞትን ለሚሹ በንኖ እንደሚጠፋ ተን ነው ይላሉ።

7ክፉዎችን ዐመፃቸው ይጠራርጋቸዋል፤

ቅን ነገር ማድረግ አይወድዱምና።

8የበደለኛ መንገድ ጠማማ ነው፤

የንጹሕ ሰው ጠባይ ግን ቀና ነው።

9ከጨቅጫቃ ሚስት ጋር በአንድ ቤት ከመኖር፣

በጣራ ላይ ጥግ ይዞ መኖር ይሻላል።

10ክፉ ሰው ክፋትን አጥብቆ ይመኛል፤

ባልንጀራውም ከእርሱ ዘንድ ርኅራኄን አያገኝም።

11ፌዘኛ ሲቀጣ፣ አላዋቂ ጥበብን ያተርፋል፤

ጠቢብ ሰው ቢማር ዕውቀትን ያገኛል።

12ጻድቁ21፥12 ወይም ጻድቁ ሰው የክፉዎችን ቤት ልብ ብሎ ይመለከታል፤

ክፉዎችንም ያጠፋቸዋል።

13ሰው የድኾችን ጩኸት ላለመስማት ጆሮውን ቢዘጋ፣

እርሱም ይጮኻል፤ መልስም አያገኝም።

14በስውር የተደረገ ስጦታ ቍጣን ያበርዳል፤

በጕያ የተሸሸገ እጅ መንሻም ታላቅ ቍጣን ጸጥ ያደርጋል።

15ፍትሕ ሲሰፍን ጻድቁን ደስ ያሰኘዋል፤

ክፉ አድራጊዎችን ግን ያሸብራል።

16የማስተዋልን መንገድ የሚስት ሰው፣

በሙታን ጉባኤ ያርፋል።

17ቅንጦትን የሚወድድ ይደኸያል፤

የወይን ጠጅና ዘይት የሚወድድም ባለጠጋ አይሆንም።

18ክፉ ሰው ለጻድቅ፣

ወስላታም ለቅን ሰው ወጆ ይሆናል።

19ከጨቅጫቃና ከቍጡ ሚስት ጋር ከመኖር፣

በምድረ በዳ መኖር ይሻላል።

20በጠቢብ ቤት ምርጥ ምግብና ዘይት ተከማችቶ ይገኛል፤

ተላላ ሰው ግን ያለ የሌለውን ያሟጥጣል።

21ጽድቅንና ፍቅርን የሚከተል፤

ሕይወትን ብልጽግናንና21፥21 ወይም ጽድቅን ክብርን ያገኛል።

22ጠቢብ የኀያላንን ከተማ ቅጥር ጥሶ ይገባል፤

መታመኛ ምሽጋቸውንም ያፈርሳል።

23አንደበቱንና ምላሱን የሚቈጣጠር፣

ራሱን ከመቅሠፍት ይጠብቃል።

24ትዕቢተኛና ኵሩ ሰው “ፌዘኛ” ይባላል፤

በጠባዩም እብሪተኛ ነው።

25ታካችን የሚገድለው ምኞቱ ነው፤

እጆቹ መሥራት አይፈልጉምና።

26ክፉ ሰው ቀኑን ሙሉ ይመኛል፤

ጻድቅ ግን አንዳች ሳያስቀር ይሰጣል።

27የክፉ ሰው መሥዋዕት አስጸያፊ ነው፤

በክፉ ዐላማ ሲያቀርብማ የቱን ያህል አስከፊ ይሆን!

28ሐሰተኛ ምስክር ይጠፋል፤21፥28 ወይም የታዛዥ ሰው ቃል ግን ጸንቶ ይኖራል

እውነቱን የሚናገር ግን ጸንቶ ይኖራል።

29ክፉ ሰው በዐጕል ድፍረት ይቀርባል፤

ቅን ሰው ግን አደራረጉን ያስተውላል።

30እግዚአብሔርን ለመቋቋም የሚያስችል፣

አንዳችም ጥበብ፣ ማስተዋልና ዕቅድ የለም።

31ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤

ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

King James Version

Proverbs 21:1-31

1The king’s heart is in the hand of the LORD, as the rivers of water: he turneth it whithersoever he will. 2Every way of a man is right in his own eyes: but the LORD pondereth the hearts. 3To do justice and judgment is more acceptable to the LORD than sacrifice. 4An high look, and a proud heart, and the plowing of the wicked, is sin.21.4 An…: Heb. Haughtiness of eyes21.4 the plowing: or, the light 5The thoughts of the diligent tend only to plenteousness; but of every one that is hasty only to want. 6The getting of treasures by a lying tongue is a vanity tossed to and fro of them that seek death. 7The robbery of the wicked shall destroy them; because they refuse to do judgment.21.7 destroy…: Heb. saw them, or, dwell with them 8The way of man is froward and strange: but as for the pure, his work is right. 9It is better to dwell in a corner of the housetop, than with a brawling woman in a wide house.21.9 a brawling…: Heb. a woman of contentions21.9 a wide…: Heb. an house of society 10The soul of the wicked desireth evil: his neighbour findeth no favour in his eyes.21.10 findeth…: Heb. is not favoured 11When the scorner is punished, the simple is made wise: and when the wise is instructed, he receiveth knowledge. 12The righteous man wisely considereth the house of the wicked: but God overthroweth the wicked for their wickedness. 13Whoso stoppeth his ears at the cry of the poor, he also shall cry himself, but shall not be heard. 14A gift in secret pacifieth anger: and a reward in the bosom strong wrath. 15It is joy to the just to do judgment: but destruction shall be to the workers of iniquity. 16The man that wandereth out of the way of understanding shall remain in the congregation of the dead. 17He that loveth pleasure shall be a poor man: he that loveth wine and oil shall not be rich.21.17 pleasure: or, sport 18The wicked shall be a ransom for the righteous, and the transgressor for the upright. 19It is better to dwell in the wilderness, than with a contentious and an angry woman.21.19 in…: Heb. in the land of the desert 20There is treasure to be desired and oil in the dwelling of the wise; but a foolish man spendeth it up. 21He that followeth after righteousness and mercy findeth life, righteousness, and honour. 22A wise man scaleth the city of the mighty, and casteth down the strength of the confidence thereof. 23Whoso keepeth his mouth and his tongue keepeth his soul from troubles. 24Proud and haughty scorner is his name, who dealeth in proud wrath.21.24 in proud…: Heb. in the wrath of pride

25The desire of the slothful killeth him; for his hands refuse to labour. 26He coveteth greedily all the day long: but the righteous giveth and spareth not. 27The sacrifice of the wicked is abomination: how much more, when he bringeth it with a wicked mind?21.27 with…: Heb. in wickedness? 28A false witness shall perish: but the man that heareth speaketh constantly.21.28 A…: Heb. A witness of lies 29A wicked man hardeneth his face: but as for the upright, he directeth his way.21.29 directeth: or, considereth

30There is no wisdom nor understanding nor counsel against the LORD. 31The horse is prepared against the day of battle: but safety is of the LORD.21.31 safety: or, victory