ምሳሌ 15 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 15:1-33

1የለዘበ መልስ ቍጣን ያበርዳል፤

ክፉ ቃል ግን ቍጣን ይጭራል።

2የጠቢብ አንደበት ዕውቀትን ታወድሳለች፤

የተላሎች አንደበት ግን ቂልነትን ያፈልቃል።

3የእግዚአብሔር ዐይኖች በሁሉም ስፍራ ናቸው፤

ክፉዎችንም ደጎችንም ነቅተው ይመለከታሉ።

4ፈውስ የምታመጣ ምላስ የሕይወት ዛፍ ናት፤

አታላይ ምላስ ግን መንፈስን ትሰብራለች።

5ተላላ የአባቱን ምክር ይንቃል፤

መታረምን የሚቀበል ግን አስተዋይነቱን ያሳያል።

6የጻድቃን ቤት በብዙ ሀብት የተሞላ ነው፤

የክፉዎች ገቢ ግን መከራን ታመጣባቸዋለች።

7የጠቢባን ከንፈር ዕውቀትን ታስፋፋለች፤

የተላሎች ልብ ግን እንዲህ አይደለም።

8እግዚአብሔር የክፉዎችን መሥዋዕት ይጸየፋል፤

የቅኖች ጸሎት ግን ደስ ያሰኘዋል።

9እግዚአብሔር የክፉዎችን መንገድ ይጸየፋል፤

ጽድቅን የሚከታተሉትን ግን ይወድዳቸዋል።

10ከመንገድ የሚወጣ ሰው ጥብቅ ቅጣት ይጠብቀዋል፤

ዕርምትን የሚጠላ ይሞታል።

11ሲኦልና የሙታን ዓለም15፥11 በዕብራይስጡ ሲኦልና አባዶን ይላል። በእግዚአብሔር ፊት የተገለጡ ናቸው፤

የሰዎች ልብማ የቱን ያህል የታወቀ ነው!

12ፌዘኛ መታረምን ይጠላል፤

ጠቢባንንም አያማክርም።

13ደስተኛ ልብ ፊትን ያፈካል፤

የልብ ሐዘን ግን መንፈስን ይሰብራል።

14አስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይሻል፤

የተላላ አፍ ግን ቂልነትን ያመነዥካል።

15የተጨቈኑ ሰዎች ዘመናቸው ሁሉ የከፋ ነው፤

በደስታ የተሞላ ልብ ግን የማይቋረጥ ፈንጠዝያ አለው።

16እግዚአብሔርን ከመፍራት ጋር ያለ ጥቂት ነገር፣

ሁከት ካለበት ትልቅ ሀብት ይበልጣል።

17ፍቅር ባለበት ጐመን መብላት፣

ጥላቻ ባለበት የሰባ ፍሪዳ ከመብላት ይሻላል።

18ግልፍተኛ ሰው ጠብ ያነሣሣል፤

ታጋሽ ሰው ግን ጠብን ያበርዳል።

19የሀኬተኛ መንገድ በእሾኽ የታጠረች ናት፤

የቅኖች መንገድ ግን የተጠረገ አውራ ጐዳና ነው።

20ጠቢብ ልጅ አባቱን ደስ ያሰኛል፤

ተላላ ሰው ግን እናቱን ይንቃል።

21ማመዛዘን የጐደለው ሰው ቂልነት ያስደስተዋል፤

አስተዋይ ሰው ግን ቀጥተኛውን መንገድ ይከተላል።

22ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤

በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።

23ሰው ተገቢ መልስ በመስጠት ደስታን ያገኛል፤

በወቅቱም የተሰጠ ቃል ምንኛ መልካም ነው!

24ወደ ሲኦል15፥24 ወይም መቃብር ከመውረድ እንዲድን፣

የሕይወት መንገድ ጠቢቡን ሰው ወደ ላይ ትመራዋለች።

25እግዚአብሔር የትዕቢተኛውን ቤት ያፈርሰዋል፤

የመበለቲቱን ዳር ድንበር ግን እንዳይደፈር ይጠብቃል።

26እግዚአብሔር የክፉውን ሰው ሐሳብ ይጸየፋል፤

የንጹሓን ሐሳብ ግን ደስ ያሰኘዋል።

27ስስታም ሰው በቤተ ሰቡ ላይ ችግር ያመጣል፤

ጕቦን የሚጠላ ግን በሕይወት ይኖራል።

28የጻድቅ ሰው ልብ የሚሰጠውን መልስ ያመዛዝናል፤

የክፉ ሰው አፍ ግን ክፋትን ያጐርፋል።

29እግዚአብሔር ከክፉዎች ሩቅ ነው፤

የጻድቃንን ጸሎት ግን ይሰማል።

30ብሩህ ገጽታ ልብን ደስ ያሰኛል፤

መልካም ዜናም ዐጥንትን ያለመልማል።

31ሕይወት ሰጭ የሆነውን ተግሣጽ የሚሰማ፣

በጠቢባን መካከል ይኖራል።

32ተግሣጽን የሚንቅ ራሱን ይንቃል፤

ዕርምትን የሚቀበል ግን ማስተዋልን ያገኛል።

33እግዚአብሔርን መፍራት ጥበብን መማር ነው፤15፥33 ወይም ጥበብ እግዚአብሔርን መፍራት ታስተምራለች።

ትሕትናም ክብርን ትቀድማለች።

New Serbian Translation

Приче Соломонове 15:1-33

1Благи одговор утишава гнев,

а груба реч покреће јарост.

2Језик мудрих добро влада знањем,

а уста безумних бљују безумљем.

3Господње су очи на свакоме месту,

мотрећи на зле и на добре.

4Здрав је језик ко дрво живота,

а дух слама језик поган.

5Безумник презире опомену свога оца,

а разборит је ко мари за укор.

6Велико је благо у дому праведника,

а злобнику је мука да заради.

7Знање расипају уста мудрих људи,

што не чини срце безумника.

8Гадна је Господу жртва зликоваца,

молитва честитих њему је милина.

9Господу је мрзак пут злобника,

а воли онога који правду следи.

10Немило је поучење за онога ко се одриче пута,

а умреће онај ко мрзи прекор.

11Пред Господом су и Свет мртвих и трулеж мртвих,

а камоли срца људских потомака.

12Подругљивац не воли онога који га кори

и не иде код мудрих људи.

13Весело срце ведри лице,

жалосно срце слама дух.

14Разборито срце тежи знању,

а уста се безумника безумљем хране.

15Немили су сви дани невољника,

а човек се доброг срца гости непрестано.

16Боље је и мало у богобојазности,

него благо силно и са њим стрепња.

17Бољи је тањир поврћа у љубави,

него утовљени во у мржњи.

18Гневан човек распаљује свађу,

а смирени човек утишава сукоб.

19Пут ленштине је обрастао трњем,

а пут је честитих поравнан.

20Мудар син радује оца,

а безуман човек презире мајку своју.

21Безумника радује безумље,

а разборит човек равно иде путем.

22Науми се изјалове кад нема савета,

а остваре с мноштвом саветника.

23Човек се радује кад одговори тачно;

како је добра реч у право време!

24Стаза живота за разумног према горе води,

и не да му према доле, у Свет мртвих да скрене.

25Господ руши кућу гордих људи

и јача међу удовице.

26Намере зликовца гадне су Господу,

а чисте су му речи љубазности.

27Кући својој беду наваљује ко нечасно и лакомо стиче,

а живеће онај човек ком се мито гади.

28Срце праведника промишља одговор,

а уста покварених људи злом бљују.

29Господ је далеко од покварењака,

а слуша молитву праведника.

30Бистар поглед и срце весели,

а добре вести подмлађују кости.

31Ухо које слуша поуку живота,

трајаће у друштву мудрих људи.

32Ко не мари за опомену, презире сам себе,

а ко слуша укор стиче разборитост.

33Богобојазност је поука мудрости,

а пре части долази понизност.