ማቴዎስ 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 9:1-38

የሽባው ሰው መፈወስ

9፥2-8 ተጓ ምብ – ማር 2፥3-12ሉቃ 5፥18-26

1ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ባሕሩን በጀልባ ተሻግሮ ወደ ራሱ ከተማ መጣ። 2በዚያም ሰዎች አንድ ሽባ ሰው በቃሬዛ ተሸክመው ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፣ “አይዞህ አንተ ልጅ፤ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል” አለው።

3በዚህን ጊዜ የአይሁድ ሃይማኖት መምህራን፣ “ይህማ እግዚአብሔርን መሳደብ ነው” በማለት በልባቸው አጕረመረሙ።

4ኢየሱስ ሐሳባቸውን ተረድቶ እንዲህ አለ፤ “ክፉ ነገር በልባችሁ ለምን ታስባላችሁ? 5ለመሆኑ፣ ‘ኀጢአትህ ይቅር ተብሎልሃል’ ከማለትና ‘ተነሥተህ ሂድ’ ከማለት የቱ ይቀልላል? 6ነገር ግን የሰው ልጅ በምድር ላይ ኀጢአትን የማስተስረይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ ነው” ብሎ፣ ሽባውን፣ “ተነሣ! ቃሬዛህን ይዘህ ወደ ቤትህ ሂድ” አለው። 7ሽባውም ተነሥቶ ወደ ቤቱ ሄደ። 8ሕዝቡም ይህን ባዩ ጊዜ ተደነቁ፣ በፍርሀት ተሞልተው፣ እንደዚህ ያለ ሥልጣን ለሰው የሰጠውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

የማቴዎስ መጠራት

9፥9-13 ተጓ ምብ – ማር 2፥14-17ሉቃ 5፥27-32

9ኢየሱስ ከዚያ ተነሥቶ ሲሄድ ማቴዎስ የሚባል አንድ ሰው በቀረጥ ማስከፈያ ኬላ ተቀምጦ አየ፤ “ተከተለኝ” አለው፤ እርሱም ተነሥቶ ተከተለው።

10ኢየሱስ በማቴዎስ ቤት በማእድ ላይ ሳለ፣ ብዙ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና ኀጢአተኞች መጥተው ከእርሱና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብረው ሊበሉ ተቀመጡ። 11ፈሪሳውያንም ይህን ባዩ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፣ “መምህራችሁ ከቀረጥ ሰብሳቢዎችና ከኀጢአተኞች ጋር እንዴት አብሮ ይበላል?” ብለው ጠየቋቸው።

12ኢየሱስም የተናገሩትን ሰምቶ እንዲህ አላቸው፤ “ሐኪም የሚያስፈልገው ለሕመምተኞች እንጂ ለጤነኞች አይደለም፤ 13ሄዳችሁ፣ ‘ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወድዳለሁ፤’ የሚለውን ቃል ትርጕም አጢኑ፤ ኀጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁምና።”

የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ያልጾሙበት ምክንያት

9፥14-17 ተጓ ምብ – ማር 2፥18-22ሉቃ 5፥33-39

14የመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ ኢየሱስ ቀርበው፣ “እኛና ፈሪሳውያን ስንጾም፣ የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን ለምን አይጾሙም?” ብለው ጠየቁት።

15ኢየሱስም እንዲህ አላችው፤ “ሙሽራው አብሯቸው እያለ ሚዜዎቹ እንዴት ሊያዝኑ ይችላሉ? ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ጊዜ ይመጣል፤ በዚያን ጊዜ ይጾማሉ።

16“በአሮጌ ልብስ ላይ አዲስ ዕራፊ የሚጥፍ ሰው የለም፤ ይህ ከሆነ አዲሱ ዕራፊ ካረጀው ልብስ ላይ ተቦጭቆ ቀዳዳውን የባሰ ያሰፋዋል። 17በአሮጌ አቍማዳ አዲስ የወይን ጠጅ ማንም አይጨምርም፤ ይህ ከሆነ አቍማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁም ይፈስሳል፤ አቍማዳውም ከጥቅም ውጭ ይሆናል። ነገር ግን አዲስ የወይን ጠጅ በአዲስ አቍማዳ ይጨመራል፤ በዚህ ሁኔታ የወይን ጠጁና አቍማዳው በደኅና ተጠብቀው ይቈያሉ።”

ከሞት የተነሣችው ልጅና ከደም መፍሰስ የተፈወሰችው ሴት

9፥18-26 ተጓ ምብ – ማር 5፥22-43ሉቃ 8፥41-56

18ኢየሱስ ሰዎቹን በማናገር ላይ ሳለ፣ አንድ ሹም ከፊቱ ተደፍቶ፣ “ልጄ አሁን ሞተችብኝ፤ በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ጫንባት” አለው። 19ኢየሱስም ተነሥቶ አብሮት ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ተከተሉት።

20ከዚያም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሙሉ ደም እየፈሰሳት ትሠቃይ የነበረች አንዲት ሴት ከኋላው መጥታ የልብሱን ጫፍ ነካች። 21እርሷም በልቧ፣ “የልብሱን ጫፍ እንኳ ብነካ እፈወሳለሁ” ብላ ነበር።

22ኢየሱስም ወደ ኋላ ዘወር ብሎ ሴቲቱን አያትና፣ “አይዞሽ፤ ልጄ ሆይ፤ እምነትሽ አድኖሻል” አላት። ሴቲቱም ወዲያውኑ ተፈወሰች።

23ኢየሱስ ወደ ምኵራብ አለቃው ቤት እንደ ደረሰ እንቢልተኞችንና የሚንጫጫውን ሕዝብ አይቶ፣ 24“ዞር በሉ፤ ልጂቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” አላቸው፤ እነርሱ ግን ሣቁበት። 25ሕዝቡም ከወጣ በኋላ ወደ ውስጥ ገብቶ እጇን ያዘ፤ ልጂቱም ተነሥታ ቆመች። 26ወሬውም በአካባቢው ሁሉ ተሠራጨ።

የዐይነ ስውሮቹና የድዳው መፈወስ

27ኢየሱስም ከዚያ እንደ ሄደ ሁለት ዐይነ ስውሮች፣ “የዳዊት ልጅ ሆይ፤ ማረን” በማለት እየጮኹ ተከተሉት።

28ዐይነ ስውሮቹም ኢየሱስ ወደ ገባበት ቤት ተከትለው ገቡ፤ ኢየሱስም፣ “ዐይናችሁን ላበራላችሁ እንደምችል ታምናላችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

እነርሱም፣ “አዎን፣ ጌታ ሆይ፤” ብለው መለሱለት።

29ከዚያም ኢየሱስ ዐይናቸውን ዳስሶ፣ “እንደ እምነታችሁ ይሁንላችሁ” አላቸው። 30ዐይናቸውም በራ፤ ኢየሱስም፣ “ይህን ማንም እንዳያውቅ” ብሎ በጥብቅ አስጠነቀቃቸው። 31እነርሱ ግን ወጥተው በአካባቢው ሁሉ ስለ ኢየሱስ አወሩ።

32ከዚያም ሲወጡ፣ በጋኔን የተያዘ ድዳ ሰው ወደ እርሱ አመጡ። 33ጋኔኑ ከወጣለት በኋላ ድዳው መናገር ጀመረ፤ ሕዝቡም ተደንቀው፣ “እንዲህ ያለ ነገር በእስራኤል ምድር ታይቶ አያውቅም” አሉ።

34ፈሪሳውያን ግን፣ “አጋንንትን የሚያወጣው፣ በአጋንንት አለቃ ነው” አሉ።

ሠራተኞች ጥቂቶች ናቸው

35ኢየሱስ በምኵራቦቻቸው እያስተማረ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት የምሥራች እየሰበከ፣ እንዲሁም ደዌንና ሕመምን ሁሉ እየፈወሰ በከተሞቹና በመንደሮቹ ዞረ። 36ሕዝቡም እረኛ እንደሌለው በግ ተጨንቀውና ተመልካች የለሽ ሆነው ባየ ጊዜ ዐዘነላቸው። 37ደቀ መዛሙርቱንም እንዲህ አላቸው፤ “መከሩ ብዙ ነው፤ የመከሩ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ 38ስለዚህ የመከሩ ጌታ፣ ወደ መከሩ ሠራተኞችን እንዲልክ ለምኑት።”

Thai New Contemporary Bible

มัทธิว 9:1-38

พระเยซูทรงรักษาคนเป็นอัมพาต

(มก.2:3-12; ลก.5:18-26)

1พระเยซูจึงเสด็จลงเรือข้ามฟากไปยังเมืองของพระองค์ 2มีผู้หามคนเป็นอัมพาตซึ่งนอนอยู่บนที่นอนมาหาพระเยซู เมื่อทรงเห็นความเชื่อของพวกเขาก็ตรัสกับคนเป็นอัมพาตนั้นว่า “ลูกเอ๋ยจงชื่นใจเถิด บาปของเจ้าได้รับการอภัยแล้ว”

3พวกธรรมาจารย์บางคนได้ยินเช่นนั้นก็คิดในใจว่า “ชายคนนี้กำลังพูดหมิ่นประมาทพระเจ้า!”

4พระเยซูทรงทราบความคิดของเขาจึงตรัสว่า “เหตุใดพวกท่านจึงคิดชั่วอยู่ในใจ? 5ที่จะพูดว่า ‘บาปของท่านได้รับการอภัยแล้ว’ กับ ‘จงลุกขึ้นเดินไป’ อย่างไหนจะง่ายกว่ากัน? 6แต่ทั้งนี้ก็เพื่อให้พวกท่านรู้ว่าบุตรมนุษย์มีสิทธิอำนาจในโลกที่จะอภัยบาป” แล้วพระองค์ตรัสกับคนเป็นอัมพาตว่า “จงลุกขึ้นแบกที่นอนกลับไปบ้านเถิด” 7และชายคนนั้นก็ลุกขึ้นกลับไปบ้าน 8เมื่อฝูงชนเห็นดังนี้ก็ยำเกรงและสรรเสริญพระเจ้าผู้ประทานสิทธิอำนาจเช่นนี้แก่มนุษย์

ทรงเรียกมัทธิว

(มก.2:14-17; ลก.5:27-32)

9เมื่อพระเยซูเสด็จจากที่นั่น พระองค์ทรงเห็นชายคนหนึ่งชื่อ มัทธิวนั่งอยู่ที่ด่านเก็บภาษี จึงตรัสกับเขาว่า “จงตามเรามา” มัทธิวก็ลุกขึ้นติดตามพระองค์ไป

10ขณะพระเยซูเสวยพระกระยาหารที่บ้านของมัทธิว คนเก็บภาษีและ “คนบาป” หลายคนมาร่วมรับประทานกับพระองค์และเหล่าสาวก 11เมื่อพวกฟาริสีเห็นเช่นนั้นก็ถามสาวกของพระองค์ว่า “ทำไมอาจารย์ของท่านจึงรับประทานอาหารร่วมกับคนเก็บภาษีและ ‘คนบาป’?”

12เมื่อพระเยซูทรงได้ยินเช่นนี้จึงตรัสว่า “คนสุขภาพดีไม่ต้องการหมอ แต่คนป่วยต้องการ 13จงไปศึกษาให้เข้าใจความหมายของข้อความที่ว่า ‘เราประสงค์ความเมตตา ไม่ใช่เครื่องบูชา’9:13 ฮชย. 6:6 เพราะเราไม่ได้มาเพื่อเรียกคนชอบธรรม แต่มาเพื่อเรียกคนบาป”

ถามพระเยซูเรื่องการถืออดอาหาร

(มก.2:18-22; ลก.5:33-39)

14ฝ่ายสาวกของยอห์นมาทูลถามพระองค์ว่า “พวกข้าพระองค์กับพวกฟาริสีถืออดอาหาร แต่ทำไมสาวกของพระองค์ไม่ถืออดอาหาร?”

15พระเยซูทรงตอบว่า “จะให้แขกของเจ้าบ่าวทุกข์โศกขณะเจ้าบ่าวอยู่ด้วยได้อย่างไร? สักวันหนึ่งเจ้าบ่าวจะถูกนำตัวไปจากเขาแล้วพวกเขาจะอดอาหาร

16“ไม่มีใครเอาผ้าใหม่ที่ยังไม่หดไปปะเสื้อผ้าเก่าเพราะผ้าใหม่จะหดรั้งผ้าเก่าให้ขาดมากกว่าเดิม 17และไม่มีใครเทเหล้าองุ่นใหม่ใส่ถุงหนังเก่า ถ้าทำเช่นนั้นถุงหนังจะขาด เหล้าองุ่นจะไหลออกมาหมด และถุงหนังจะเสียหาย ไม่หรอก เขาย่อมเทเหล้าองุ่นใหม่ใส่ในถุงหนังใหม่และเก็บรักษาไว้ได้ทั้งสองอย่าง”

เด็กที่เสียชีวิตและหญิงที่ป่วย

(มก.5:22-43; ลก.8:41-56)

18ขณะที่พระองค์ตรัสอยู่นั้น นายธรรมศาลาคนหนึ่งมาคุกเข่าทูลพระองค์ว่า “ลูกสาวของข้าพระองค์เพิ่งเสียชีวิต แต่ขอโปรดเสด็จไปทรงวางมือให้แล้วเธอจะเป็นขึ้นมา” 19พระเยซูทรงลุกขึ้นไปกับเขาเหล่าสาวกก็ไปด้วย

20ขณะนั้นเองหญิงคนหนึ่งซึ่งตกเลือดเรื้อรังมาสิบสองปีแล้วได้เข้ามาข้างหลังพระองค์และแตะชายฉลองพระองค์ 21นางคิดในใจว่า “ถ้าเพียงแต่เราแตะฉลองพระองค์ เราก็จะหายโรค”

22พระเยซูทรงหันมาเห็นนางจึงตรัสว่า “ลูกสาวเอ๋ย จงชื่นใจเถิด ความเชื่อของเจ้าทำให้เจ้าหายโรคแล้ว” นางก็หายโรคตั้งแต่วินาทีนั้น

23เมื่อพระเยซูเสด็จเข้าไปในบ้านของนายธรรมศาลาแล้วทรงเห็นพวกเป่าปี่และผู้คนส่งเสียงอึกทึก 24พระองค์ก็ตรัสว่า “ไปเสียเถิด เด็กหญิงนี้ยังไม่ตาย เพียงแต่หลับอยู่” แต่พวกเขาพากันหัวเราะเยาะพระองค์ 25หลังจากผู้คนออกไปแล้ว พระองค์ทรงเข้ามาจับมือเด็กน้อย เด็กหญิงนั้นก็ลุกขึ้น 26ข่าวนี้จึงเลื่องลือไปทั่วแคว้น

พระเยซูทรงรักษาคนตาบอดและคนใบ้

27ขณะพระเยซูเสด็จจากที่นั่น มีชายตาบอดสองคนเดินตามพระองค์มาพลางร้องว่า “บุตรดาวิดเจ้าข้า เมตตาพวกข้าพระองค์ด้วยเถิด!”

28เมื่อทรงเข้าไปในบ้านแล้ว คนตาบอดทั้งสองก็มาหาพระองค์ พระเยซูตรัสถามเขาว่า “ท่านเชื่อหรือว่าเราสามารถทำการนี้ได้?”

ทั้งสองทูลตอบว่า “เชื่อ พระเจ้าข้า”

29พระองค์จึงทรงแตะตาของพวกเขาและตรัสว่า “ให้เป็นไปตามความเชื่อของเจ้าเถิด” 30ทั้งสองก็กลับมองเห็นได้ พระเยซูทรงกำชับเขาอย่างหนักแน่นว่า “อย่าให้ใครรู้เรื่องนี้” 31แต่เขาก็ออกไปป่าวประกาศข่าวเกี่ยวกับพระองค์ทั่วแคว้น

32ขณะที่พวกเขากำลังจะพากันออกไป มีคนนำชายผู้หนึ่งซึ่งถูกผีสิงและพูดไม่ได้มาพบพระเยซู 33และเมื่อทรงขับผีออกแล้ว ชายที่เคยเป็นใบ้ก็พูดได้ ประชาชนพากันประหลาดใจและพูดว่า “ไม่เคยพบเห็นอะไรเช่นนี้เลยในอิสราเอล”

34แต่พวกฟาริสีพูดว่า “เขาขับผีออกด้วยฤทธิ์ของนายผี”

คนงานยังน้อยอยู่

35พระเยซูเสด็จไปตามเมืองและหมู่บ้านต่างๆ ทรงเทศนาในธรรมศาลา ประกาศข่าวประเสริฐเรื่องอาณาจักรของพระเจ้า และรักษาโรคภัยไข้เจ็บทั้งปวง 36เมื่อพระองค์ทอดพระเนตรเห็นประชาชนก็ทรงสงสารเขาเพราะพวกเขาถูกรังควานและไร้ที่พึ่งเหมือนลูกแกะขาดคนเลี้ยง 37แล้วพระองค์ก็ตรัสกับเหล่าสาวกว่า “งานเก็บเกี่ยวมีมากแต่คนงานมีน้อยนัก 38เพราะฉะนั้นจงทูลขอพระองค์ผู้ทรงเป็นเจ้าแห่งการเก็บเกี่ยวให้ส่งคนงานมายังทุ่งแห่งการเก็บเกี่ยวของพระองค์”