ማቴዎስ 22 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 22:1-46

በሰርግ ድግስ ላይ የተጠሩ ሰዎች ምሳሌ

22፥2-14 ተጓ ምብ – ሉቃ 14፥16-24

1ኢየሱስም እንደ ገና እንዲህ የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2“መንግሥተ ሰማይ ለልጁ ሰርግ የደገሰን ንጉሥ ትመስላለች፤ 3ንጉሡም የተጋበዙትን ሰዎች እንዲጠሩ አገልጋዮቹን ላከ፤ እነርሱ ግን አንመጣም አሉ።

4“እንደ ገናም ሌሎች አገልጋዮች ልኮ፣ ‘የተጋበዙትን፣ እነሆ፣ በሬዎችንና የሠቡ ከብቶቼን ዐርጄ ድግሱን አዘጋጅቻለሁ፤ ሁሉም ነገር ዝግጁ ስለሆነ፣ ወደ ሰርጉ ኑ በሏቸው’ አለ።

5“ተጋባዦቹ ግን ጥሪውን ችላ ብለው፣ አንዱ ወደ ዕርሻው ሌላው ወደ ንግዱ ሄደ፤ 6የቀሩትም አገልጋዮቹን በመያዝ አጕላልተው ገደሏቸው። 7ንጉሡም በመቈጣት ሰራዊቱን ልኮ ገዳዮቻቸውን አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።

8“ከዚያም አገልጋዮቹን እንዲህ አላቸው፤ ‘የሰርጉ ድግስ ዝግጁ ነው፤ ነገር ግን የተጋበዙት የሚገባቸው ሆነው ስላልተገኙ፣ 9ወደ መንገድ መተላለፊያ ወጥታችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ድግስ ጥሩ።’ 10አገልጋዮቹም ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን መልካሙንም ክፉውንም ሁሉ ሰብስበው የሰርጉን አዳራሽ በእንግዶች ሞሉት።

11“ንጉሡም የተጋበዙትን እንግዶች ለማየት ሲገባ፣ አንድ የሰርግ ልብስ ያልለበሰ ሰው አየ፤ 12እንዲህም አለው፤ ‘ወዳጄ ሆይ፤ የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት እዚህ ልትገባ ቻልህ?’ ሰውየው ግን የሚመልሰው ቃል አልነበረውም።

13“ንጉሡም አገልጋዮቹን፣ ‘እጅና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጥታችሁ ጣሉት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል’ አላቸው፤ 14የተጠሩት ብዙዎች፣ የተመረጡት ግን ጥቂቶች ናቸውና።”

ግብር ስለ መክፈል

22፥15-22 ተጓ ምብ – ማር 12፥13-17ሉቃ 20፥20-26

15ከዚህ በኋላ ፈሪሳውያን ወጥተው በመሄድ በአፍ ዕላፊ እንዴት እንደሚያጠምዱት ተማከሩ። 16ደቀ መዛሙርታቸውን ከሄሮድስ ወገኖች ጋር ወደ እርሱ ልከው እንዲህ አሉት፤ “መምህር ሆይ፤ አንተ እውነተኛና የእግዚአብሔርንም መንገድ በእውነት የምታስተምር እንደ ሆንህ፣ ለማንም ሳታዳላ ሁሉን በእኩልነት እንደምትመለከት እናውቃለን፤ 17ንገረን፤ ምን ይመስልሃል? ለመሆኑ ለቄሣር ግብር መክፈል ይገባል ወይስ አይገባም?”

18ኢየሱስ ግን ተንኰላቸውን በመረዳት እንዲህ አላቸው፤ “እናንተ ግብዞች ለምን በነገር ልታጠምዱኝ ትሻላችሁ? 19ለግብር የሚከፈለውን ገንዘብ እስቲ አሳዩኝ።” እነርሱም አንድ ዲናር አመጡለት። 20እርሱም፣ “በዚህ ገንዘብ ላይ የሚታየው መልክ የማን ነው? ጽሕፈቱስ የማን ነው?” አላቸው።

21እነርሱም፣ “የቄሣር ነው” አሉት።

እርሱም መልሶ፣ “እንግዲያውስ የቄሣርን ለቄሣር፣ የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር ስጡ” አላቸው።

22ይህን ሲሰሙ ተደነቁ፤ ትተውትም ሄዱ።

ስለ ሙታን ትንሣኤ

22፥23-33 ተጓ ምብ – ማር 12፥18-27ሉቃ 20፥27-40

23የሙታን ትንሣኤ የለም ብለው የሚያምኑ ሰዱቃውያን በዚያኑ ቀን ወደ ኢየሱስ ቀርበው እንዲህ ብለው ጠየቁት፤ 24“መምህር ሆይ፤ ሙሴ፣ ‘አንድ ሰው ከሚስቱ ልጅ ሳይወልድ ቢሞት ወንድሙ የሟቹን ሚስት አግብቶ ለእርሱ ዘር ይተካለት’ ብሏል። 25በእኛ ዘንድ ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ፤ የመጀመሪያው ሚስት አግብቶ ልጅ ሳይወልድ በመሞቱ፣ ሚስቱን ወንድሙ አገባት፤ 26እንደዚሁ ደግሞ ሁለተኛውም፣ ሦስተኛውም እስከ ሰባተኛው ድረስ በዚህ ሁኔታ ሞቱ። 27በመጨረሻ ሴትየዋ ራሷ ሞተች። 28ስለዚህ ሁሉም ስላገቧት በትንሣኤ ቀን ከሰባቱ ለየትኛው ሚስት ትሆናለች?”

29ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰ፤ “ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ትስታላችሁ፤ 30ከትንሣኤ በኋላ ሰዎች እንደ ሰማይ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፤ አይጋቡም። 31ስለ ሙታን ትንሣኤ ግን እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ የተናገራችሁን አላነበባችሁምን? 32‘እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ።’ እግዚአብሔር የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም።”

33ሕዝቡም ይህን በሰሙ ጊዜ በትምህርቱ ተደነቁ።

ታላቁ ትእዛዝ

22፥34-40 ተጓ ምብ – ማር 12፥28-31

34ኢየሱስ ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው ሰምተው፣ ፈሪሳውያን በአንድነት ተሰበሰቡ፤ 35ከእነርሱም አንድ የኦሪት ሕግ ዐዋቂ፣ ሊፈትነው ፈልጎ እንዲህ አለው፤ 36“መምህር ሆይ፤ ከሕግ ሁሉ የሚበልጠው የትኛው ትእዛዝ ነው?”

37እርሱም እንዲህ አለው፤ “ ‘ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ሐሳብህ ውደድ፤’ 38ይህ የመጀመሪያውና ከሁሉ የሚበልጠው ትእዛዝ ነው፤ 39ሁለተኛውም ያንኑ ይመስላል፤ ይህም፣ ‘ጎረቤትህን እንደ ራስህ ውደድ’ የሚለው ነው፤ 40ሕግና ነቢያት በሙሉ በእነዚህ ሁለት ትእዛዞች ላይ የተንጠለጠሉ ናቸው።”

ክርስቶስ የማን ልጅ ነው?

22፥41-46 ተጓ ምብ – ማር 12፥35-37ሉቃ 20፥41-44

41ፈሪሳውያን ተሰብስበው ሳሉ ኢየሱስ፣ እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፤ 42“ስለ ክርስቶስ22፥42 ወይም መሲሑ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው?”

እነርሱም፣ “የዳዊት ልጅ ነው” አሉት።

43እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ታዲያ፣ ዳዊት በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ለምን ‘ጌታዬ’ ይለዋል? ለምንስ፣ እንዲህ ይለዋል?

44“ ‘እግዚአብሔር ጌታዬን፤

“ጠላቶችህን ከእግርህ በታች

እስካንበረከክልህ ድረስ፣

በቀኜ ተቀመጥ።” ’

45ስለዚህ ዳዊት፣ ‘ጌታዬ’ ብሎ ከጠራው፣ እንዴት ልጁ ሊሆን ይችላል?” 46አንድ ቃል ሊመልስለት የቻለ ወይም ከዚያን ቀን ጀምሮ ሊጠይቀው የደፈረ ማንም አልነበረም።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מתי 22:1‏-46

כב

1‏-2ישוע סיפר להם משלים נוספים על מלכות השמים. ”אפשר להמשיל את מלכות השמים למלך שערך סעודת־חתונה גדולה לבנו. 3כאשר הייתה הסעודה מוכנה שלח המלך שליחים אל האורחים שהזמין, כדי להודיע להם שהגיע הזמן לבוא לסעודה, אך כולם סרבו לבוא. 4המלך שלח שליחים אחרים להודיע למוזמנים: ’הזדרזו! השורים והבקר המפוטם טבוחים והצלי כבר בתנור!‘

5”אולם המוזמנים צחקו והלכו כל אחד לענייניו, אחד לשדה ואחר לשוק 6היו גם כאלה שתקפו את השליחים, הכו אותם, התעללו בהם ואפילו רצחו אחדים מהם.

7”המלך הזועם שלח גדודי צבא כדי להרוג את הרוצחים ולשרוף את עירם. 8הוא פנה אל משרתיו ואמר: ’משתה החתונה מוכן, אולם האורחים שהוזמנו לא היו ראויים לכבוד הזה. 9צאו אל הרחובות והזמינו את כל מי שתפגשו!‘ 10המשרתים עשו כדבריו והכניסו לאולם את כל מי שפגשו: אנשים טובים ורעים גם יחד, והאולם נמלא אורחים.

11”אולם כשנכנס המלך אל האולם כדי לראות את האורחים, גילה כי אחד מהם לא לבש בגדי חתונה הולמים.

12” ’ידידי‘, שאל המלך, ’כיצד נכנסת אל האולם ללא בגדי חתונה?‘ לַאורח לא הייתה תשובה.

13”אז אמר המלך למשרתיו: ’קשרו את ידיו ורגליו והשליכוהו החוצה לחושך, למקום שבו יש רק בכי וחריקת שיניים!‘ 14כי רבים הקרואים אך מעטים הנבחרים.“

15שוב נועצו הפרושים ביניהם וחיפשו דרך להכשיל את ישוע בלשונו. 16הם החליטו לשלוח אליו כמה מאנשיהם, יחד עם אנשי הורדוס, כדי לשאול אותו שאלה. ”אדון,“ הם פתחו, ”אנחנו יודעים שאתה איש ישר, ושאתה מלמד את דבר אלוהים בלי להתחשב בתוצאות, בלי פחד ומשוא־פנים. 17אמור לנו בבקשה, האם עלינו לשלם מס לקיסר הרומאי או לא?“ 18ישוע הבין את מזימתם, ולכן ענה: ”צבועים שכמוכם! כך אתם מנסים אותי? 19בואו הנה; תנו לי מטבע.“ והם נתנו לו מטבע. 20”דמותו של מי חקוקה כאן?“ שאל אותם ישוע. ”ושל מי השם החקוק מתחת לדמות?“

21”של הקיסר“, ענו.

”אם כך, תנו לקיסר את מה ששייך לו, ותנו לאלוהים את מה ששייך לאלוהים!“

22תשובתו הפתיעה והביכה אותם, והם הסתלקו משם.

23באותו יום באו צדוקים אחדים (שאינם מאמינים בתחיית המתים) ושאלו: 24”רבי, משה אמר שאם אדם נשוי מת ואינו משאיר אחריו ילדים, חייב אחיו להתחתן עם האלמנה, כדי שתוכל ללדת בן שישא את שם המת. 25אנחנו מכירים משפחה אחת שהיו בה שבעה אחים. האח הבכור נשא אישה, וכעבור זמן קצר מת ולא השאיר אחריו בן. האלמנה נישאה לאח שני, 26אולם גם הוא נפטר ולא השאיר בן. כך נישאה האישה לאח השלישי, לרביעי וכן הלאה – עד שנישאה לכל אחד משבעת האחים. 27לבסוף מתה גם האישה. 28אם כן, למי תהיה שייכת האישה בתחיית המתים? הרי היא נישאה לכל שבעת האחים!“

29השיב להם ישוע: ”טעותכם נובעת מבורותכם בכל הנוגע לכתבי־הקודש ולגבורתו של אלוהים.“ 30”כי בתחיית המתים לא יהיו עוד נשואים; כולם יהיו כמלאכים בשמים. 31באשר לשאלתכם – אם יקומו המתים לתחייה או לא – האם לא קראתם מה אמר לכם אלוהים בתורה? 32’אנוכי אלוהי אברהם, אלוהי יצחק ואלוהי יעקב!‘ והרי אלוהים הוא אלוהי החיים ולא אלוהי המתים!“

33תשובותיו הרשימו את הקהל הנדהם, 34‏-35אך לא את הפרושים. כששמעו כיצד השתיק ישוע את הצדוקים בתשובתו, העלו במוחם שאלה אחרת. אחד מהם, דיין במקצועו, קם ושאל: 36”רבי, מה היא המצווה החשובה ביותר בתורת משה?“

37”ואהבת את ה׳ אלוהיך בכל לבבך, ובכל נפשך ובכל שכלך“, השיב ישוע. 38”זאת המצווה הראשונה והחשובה ביותר! 39והמצווה השנייה דומה לה: ’ואהבת לרעך כמוך‘. 40כל יתר המצוות וכל דברי הנביאים מבוססים על שתי מצוות אלה. אם באמת תקיים את שתי המצוות אלה, תקיים למעשה את התורה כולה.“

41בעוד הפרושים נקהלים סביבו, שאל אותם ישוע שאלה: 42”מה בדבר המשיח? בנו של מי הוא?“

”הוא בן־דוד“, השיבו הפרושים.

43”אם כך, מדוע קורא לו דוד בהשראת רוח הקודש ’אדון‘?“ המשיך ישוע לשאול. 44”הרי דוד אמר:22‏.44 כב 44 תהלים קי 1

’נאם ה׳ לאדני,

שב לימיני עד אשית אויביך הדם לרגליך‘.

45ואם דוד קורא לו ’אדון‘, כיצד הוא יכול להיות בנו?“

46לא הייתה להם תשובה, ומאותו יום לא העז איש לשאול אותו שאלות מכשילות.