ማቴዎስ 19 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 19:1-30

ስለ መፋታት የቀረበ ጥያቄ

19፥1-9 ተጓ ምብ – ማር 10፥1-12

1ኢየሱስ ይህን ተናግሮ ከጨረሰ በኋላ፣ ገሊላን ትቶ ከዮርዳኖስ ማዶ ወዳለው ወደ ይሁዳ አውራጃ ሄደ። 2ብዙ ሕዝብም ተከተለው፤ በዚያም ፈወሳቸው።

3ፈሪሳውያንም ሊፈትኑት ቀርበው፣ “ለመሆኑ ለአንድ ሰው በማንኛውም ምክንያት ሚስቱን መፍታት ተፈቅዷልን?” ሲሉ ጠየቁት።

4እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “ፈጣሪ በመጀመሪያ ወንድና ሴት አድርጎ እንደ ፈጠራቸው አላነበባችሁምን? 5እንዲህም አለ፤ ‘ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ ከሚስቱም ጋር ይጣመራል፣ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ’ የተባለው በዚህ ምክንያት አይደለምን? 6ከእንግዲህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ሁለት አይደሉም፤ ስለዚህ እግዚአብሔር ያጣመረውን ሰው አይለየው።”

7እነርሱም፣ “ታዲያ፣ ሙሴ አንድ ወንድ የፍቺውን የምስክር ወረቀት ሰጥቶ ሚስቱን እንዲያሰናብት ለምን አዘዘ?” አሉት።

8ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “ሙሴ የልባችሁን ጥንካሬ አይቶ ሚስቶቻችሁን እንድትፈቱ ፈቀደላችሁ እንጂ ከመጀመሪያው እንዲህ አልነበረም፤ 9እላችኋለሁ፤ በትዳሯ ላይ ዝሙት ፈጽማ እስካልተገኘች ድረስ፣ ሚስቱን ፈትቶ ሌላ ሴት የሚያገባ ሁሉ አመንዝራ ይሆናል፤ እርሷንም አመንዝራ ያደርጋታል፣ የተፈታችውንም ሴት የሚያገባ ያመነዝራል።”

10ደቀ መዛሙርቱም፣ “የባልና የሚስት ጕዳይ እንዲህ ከሆነ አለማግባት ይሻላል” አሉት።

11ኢየሱስ ግን እንዲህ አላቸው፤ “ከተሰጣቸው በስተቀር ይህን ትምህርት ማንም ሊቀበል አይችልም፤ 12ምክንያቱም አንዳንዶች ጃንደረባ ሆነው ይወለዳሉ፤ ሌሎች በሰው እጅ ተሰልበው ጃንደረባ ይሆናሉ፤ ደግሞም ለመንግሥተ ሰማይ ሲሉ ራሳቸውን ጃንደረባ የሚያደርጉ አሉ። ይህን መቀበል የሚችል ይቀበል።”

ኢየሱስ ሕፃናትን ባረካቸው

19፥13-15 ተጓ ምብ – ማር 10፥13-16ሉቃ 18፥15-17

13ከዚያም እጆቹን በላያቸው ላይ ጭኖ እንዲጸልይላቸው ሕፃናትን ወደ እርሱ አቀረቧቸው። ደቀ መዛሙርቱ ግን ሕፃናቱን ያመጡትን ሰዎች ገሠጿቸው።

14ኢየሱስም፣ “ሕፃናት ወደ እኔ ይምጡ፤ አትከልክሏቸው፤ መንግሥተ ሰማይ እንደ እነርሱ ላሉት ናትና” አላቸው። 15እጁንም ከጫነባቸው በኋላ ከዚያ ስፍራ ተነሥቶ ሄደ።

የሀብታሙ ጥያቄ

19፥16-29 ተጓ ምብ – ማር 10፥17-30ሉቃ 18፥18-30

16ከዚያም አንድ ሰው ወደ ኢየሱስ ቀርቦ፣ “መምህር ሆይ፤ የዘላለምን ሕይወት አገኝ ዘንድ ምን መልካም ነገር ልሥራ” ሲል ጠየቀው።

17ኢየሱስም፣ “ስለ መልካም ነገር ለምን ትጠይቀኛለህ? መልካም የሆነ አንዱ ብቻ ነው፤ ወደ ሕይወት ለመግባት ከፈለግህ ግን ትእዛዞቹን ጠብቅ” አለው።

18ሰውየውም፣ “የትኞቹን ትእዛዞች?” ሲል ጠየቀ።

ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “አትግደል፣ አታመንዝር፤ አትስረቅ፤ በሐሰት አትመስክር፤ 19አባትህንና እናትህን አክብር፤ ጎረቤትህን እንደ ራስህ ውደድ።”

20ጕልማሳውም ሰው፣ “እነዚህንማ ጠብቄአለሁ፤ ከዚህ ሌላ የሚጐድለኝ ምን አለ?” አለው።

21ኢየሱስም፣ “ፍጹም ለመሆን ከፈለግህ፣ ሄደህ ንብረትህን ሁሉ ሸጠህ፣ ገንዘቡን ለድኾች ስጥ፤ በሰማይም ሀብት ታገኛለህ። ከዚያም መጥተህ ተከተለኝ” አለው።

22ጕልማሳው ሰውየም ይህን ሲሰማ፣ ብዙ ሀብት ስለ ነበረው እያዘነ ሄደ።

23ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አለ፤ “እውነት እላችኋለሁ፣ ለሀብታም ወደ መንግሥተ ሰማይ መግባት እጅግ አስቸጋሪ ነው። 24ደግሜ እላችኋለሁ፤ ሀብታም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀልላል።”

25ይህን ሲሰሙ፣ ደቀ መዛሙርቱ እጅግ በመገረም፣ “እንግዲያስ ማን ሊድን ይችላል?” ሲሉ ጠየቁ።

26ኢየሱስም እየተመለከታቸው፣ “ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉም ነገር ይቻላል” አላቸው።

27ጴጥሮስም መልሶ፣ “እኛ ሁሉን ትተን ተከትለንሃል፤ ታዲያ ምን እናገኝ ይሆን?” አለው።

28ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ በሚመጣው አዲስ ዓለም የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን ላይ በሚቀመጥበት ጊዜ፣ እናንተም የተከተላችሁኝ በዐሥራ ሁለት ዙፋን ላይ ተቀምጣችሁ፣ በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ላይ ትፈርዳላችሁ። 29ስለ ስሜ ብሎ ቤቶችን፣ ወንድሞችን፣ እኅቶችን፣ አባትን፣ እናትን19፥29 አንዳንድ ቅጆች እናትን ወይም ሚስትን ይላሉ።፣ ልጆችን ወይም ዕርሻን የሚተው ሁሉ መቶ ዕጥፍ ይቀበላል፤ የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። 30ነገር ግን ብዙ ፊተኞች ኋለኞች፣ ብዙ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።

Knijga O Kristu

Matej 19:1-30

O braku i rastavi

(Mk 10:1-12; Lk 16:18)

1Kad je Isus završio s govorom, ode iz Galileje u Judeju s istočne strane rijeke Jordana. 2Za njim je pošlo silno mnoštvo te ih je on ondje iscjeljivao.

3Priđu mu neki farizeji pa ga upitaju pokušavajući ga zaskočiti: “Smije li se muž razvesti od žene zbog bilo kojeg razloga?”

4On odgovori: “Niste li u Pismu čitali da ih je Stvoritelj na početku stvorio ‘muškim i ženskim’19:4 Postanak 1:27; 5:2. 5i da je rekao: ‘Čovjek će ostaviti oca i majku da bi se sjedinio sa svojom ženom, i njih će dvoje biti jedno tijelo’?19:5 Postanak 2:24. 6Njih dvoje, prema tome, nisu više dva, nego jedno. Neka dakle nijedan čovjek ne rastavlja one koje je Bog sjedinio!”

7“Zašto je onda Mojsije rekao da muž treba ženi samo napisati otpusnicu pa se može razvesti?”19:7 Ponovljeni zakon 24:1. upitaju.

8Isus im odgovori: “Mojsije je učinio taj ustupak da možete otpustiti svoju ženu zbog vaših tvrdih srca, ali u početku nije bilo tako. 9Ali ja vam kažem: Tko god se razvede od svoje žene, osim zbog njezina bluda—pa se oženi drugom, čini preljub.”19:9 U nekim rukopisima još stoji: I onaj tko se oženi razvedenicom, čini preljub.

10Nato će Isusovi učenici: “Ako je između muža i žene tako, onda je bolje ne ženiti se!”

11“Ne mogu to razumjeti svi, nego samo oni kojima je dano”, reče im Isus. 12“Ima ljudi koji su od rođenja nesposobni za ženidbu, ima ih koje su ljudi za to onesposobili, a neki se dragovoljno odriču ženidbe zaradi nebeskoga kraljevstva. Tko može shvatiti, neka shvati!”

Isus blagoslivlja djecu

(Mk 10:13-16; Lk 18:15-17)

13Tada mu dovodili djecu da na njih stavi ruke i da se pomoli. Učenici su im to priječili. 14Isus im nato reče: “Pustite dječicu k meni i ne tjerajte ih jer takvima pripada nebesko kraljevstvo!” 15Položi na njih ruke, a zatim ode odande.

Isus i bogataš

(Mk 10:17-31; Lk 18:18-30)

16Priđe mu neki čovjek i upita: “Učitelju, koje dobro moram činiti da bih zadobio vječni život?”

17Isus mu reče: “Zašto me pitaš o dobrome? Samo je jedan dobar—Bog! Ali ako želiš ući u život, ispunjaj zapovijedi!”

18“Koje?” upita on.

Isus odgovori: “Ne ubij”, “Ne čini preljub”, “Ne ukradi”, “Ne svjedoči lažno”, 19“Poštuj oca i majku i ljubi bližnjega svoga kao samoga sebe!”19:18-19 Izlazak 20:12-16; Levitski zakonik 19:18; Ponovljeni zakon 5:16-20.

20“Sve sam to činio”, reče mu mladić. “Što mi još nedostaje?”

21“Želiš li biti savršenim,” odgovori Isus, “idi i prodaj sve što imaš, a novac razdijeli siromasima pa ćeš imati blago na nebu. Onda dođi i slijedi me!” 22Kad je mladić to čuo, se ražalosti i ode jer je imao veliki imetak.

23Isus nato reče učenicima: “Zaista vam kažem, teško je bogatašu ući u nebesko kraljevstvo! 24I opet vam kažem: Lakše bi devi bilo provući se kroz iglenu ušicu nego bogatašu ući u Božje kraljevstvo!”

25Učenici se zaprepaste. “Pa tko se onda uopće može spasiti?” pitali su.

26Isus ih pozorno pogleda pa reče: “Ljudima je to potpuno nemoguće, ali ne i Bogu. Ali Bogu je sve moguće!”

27Tada mu Petar reče: “Evo, mi smo sve ostavili da te slijedimo. Što ćemo za to dobiti?”

28Isus odgovori: “Zaista vam kažem, kada ja, Sin Čovječji, sjednem o obnovi svijeta na svoje slavno prijestolje, vi ćete sjesti na dvanaest prijestolja i suditi dvanaest Izraelovih plemena. 29A svatko tko zaradi mene ostavi kuću, ili braću, ili sestre, ili oca, ili majku, ili ženu, ili djecu, ili njive, primit će stostruko i baštiniti vječni život. 30Ali mnogi koji su sada prvi tada će biti na zadnjemu mjestu, a mnogi koje ovdje smatraju zadnjima ondje će biti najveći.”