ማቴዎስ 14 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 14:1-36

የመጥምቁ ዮሐንስ መሞት

14፥1-12 ተጓ ምብ – ማር 6፥14-29

1በዚያን ጊዜ የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረው፣ ሄሮድስ ስለ ኢየሱስ ዝና ሰማ፤ 2ባለሟሎቹንም፣ “እንዲህ ከሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ከሞት ተነሥቶ መጥቷል ማለት ነው፤ ይህ ሁሉ ድንቅ ታምራት በእርሱ የሚደረገውም ለዚህ ነው” አላቸው።

3ቀደም ሲል ሄሮድስ፣ በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ዮሐንስን አስይዞ ወህኒ አስገብቶት ነበር። 4ምክንያቱም ዮሐንስ፣ “እርሷን እንድታገባ ሕግ አይፈቅድልህም” ይለው ነበር። 5ሄሮድስም ዮሐንስን ሊገድለው ፈልጎ፣ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ይመለከተው ስለ ነበር ፈራ።

6ሄሮድስ የልደቱን ቀን ሲያከብር፣ የሄሮድያዳ ልጅ በዘፈን ደስ ስላሰኘችው፣ 7የምትጠይቀውን ሁሉ ሊሰጣት በመሐላ ቃል ገባላት። 8ልጅቷም በእናቷ ተመክራ፣ “የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ በሳሕን ላይ አድርገህ አሁኑኑ ስጠኝ” አለችው። 9በዚህ ጊዜ ንጉሡ ዐዘነ፤ ይሁን እንጂ ስለ መሐላውና ከእርሱ ጋር ስለ ነበሩ እንግዶች ሲል ጥያቄዋ እንዲፈጸምላት አዘዘ። 10ልኮም በወህኒ ውስጥ እንዳለ የዮሐንስን ራስ አስቈረጠ። 11የተቈረጠውንም ራስ በሳሕን ላይ አድርገው ለልጂቱ ሰጧት፤ ልጂቱም ወስዳ ለእናቷ ሰጠች። 12የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትም አስከሬኑን ወስደው ቀበሩት፤ ከዚያም ሄደው ለኢየሱስ ነገሩት።

ኢየሱስም አምስት ሺሕ ሰዎችን በታምር መገበ

14፥13-21 ተጓ ምብ – ማር 6፥32-44ሉቃ 9፥10-17ዮሐ 6፥1-13

14፥13-21 ተጓ ምብ – ማቴ 15፥32-38

13ኢየሱስ የሆነውን ነገር በሰማ ጊዜ፣ ከነበረበት ተነሥቶ ወደ አንድ ገለልተኛ ስፍራ በጀልባ ሄደ። ሕዝቡም ይህን ሰምተው፣ ከየከተማው በእግር ተከተሉት። 14ኢየሱስም ከጀልባው ሲወርድ ብዙ ሕዝብ አይቶ ራራላቸው፤ ሕመምተኞቻቸውንም ፈወሰላቸው።

15እየመሸ በመሄዱም ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው፣ “ይህ ስፍራ ምንም የማይገኝበት ምድረ በዳ ነው፤ ጊዜው እየመሸ ስለሆነ፣ ወደ መንደሮች ሄደው የሚበሉት ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት” አሉት።

16ኢየሱስ ግን፣ “መሄድ አያስፈልጋቸውም፤ የሚበሉትን እናንተ ስጧቸው” አላቸው።

17እነርሱም፣ “በዚህ ያለን አምስት እንጀራና ሁለት ዓሣ ብቻ ነው” አሉት።

18እርሱም፣ “እስቲ ያለውን ወደ እኔ አምጡት” አላቸው። 19ከዚያም ሕዝቡ በሣሩ ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፤ አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ዐይኑን ወደ ሰማይ በማቅናት አመስግኖና ባርኮ እንጀራውን ቈረሰ፤ ለደቀ መዛሙርቱም ሰጠ፤ እነርሱም ለሕዝቡ ሰጡ። 20ሁሉም በልተው ጠገቡ፤ ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ የተረፈውን ቍርስራሽ ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ አነሡ። 21የበሉትም ከሴቶችና ከሕፃናት ሌላ፣ አምስት ሺሕ ወንዶች ያህሉ ነበር።

ኢየሱስ በባሕር ላይ በእግሩ ሄደ

14፥22-33 ተጓ ምብ – ማር 6፥45-51ዮሐ 6፥15-21

14፥34-36 ተጓ ምብ – ማር 6፥53-56

22ወዲያውኑ ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ተሳፍረው ወደ ማዶ እንዲቀድሙት አዘዛቸውና እርሱ ሕዝቡን ለማሰናበት ወደ ኋላ ቀረት አለ። 23ሕዝቡን ካሰናበተ በኋላም ለመጸለይ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ፤ በጨለመም ጊዜ ብቻውን በዚያው ነበር፤ 24በዚያ ጊዜ ጀልባዋ ባሕሩን ዘልቃ14፥24 ግሪኩ ብዙ ምዕራፍ ይላል። እየተጓዘች ሳለች ነፋስ ተነሥቶ በማዕበል ትንገላታ ጀመር።

25ከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል ኢየሱስ በባሕሩ ላይ እየተራመደ ደቀ መዛሙርቱ ወዳሉበት መጣ። 26ደቀ መዛሙርቱም በባሕሩ ላይ እየተራመደ ሲመጣ ባዩት ጊዜ ፈሩ፤ እነርሱም፣ “ምትሀት ነው!” በማለት በፍርሀት ጮኹ።

27ኢየሱስም ወዲያውኑ፣ “አይዟችሁ፤ እኔ ነኝ አትፍሩ” አላቸው።

28ጴጥሮስም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ከሆንህስ፣ በውሃው ላይ እየተራመድሁ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ” አለው።

29እርሱም፣ “ና” አለው።

ጴጥሮስም፣ ከጀልባው ወርዶ በውሃው ላይ እየተራመደ ወደ ኢየሱስ አመራ። 30ነገር ግን የነፋሱን ኀይል ባየ ጊዜ ፈራ፤ መስጠምም ሲጀምር፣ “ጌታ ሆይ፤ አድነኝ!” ብሎ ጮኸ።

31ኢየሱስም ወዲያውኑ እጁን ዘርግቶ ያዘውና፣ “አንተ እምነት የጐደለህ፤ ለምን ተጠራጠርህ?” አለው።

32ኢየሱስና ጴጥሮስ ጀልባው ላይ እንደ ወጡ ነፋሱ ጸጥ አለ። 33ከዚያም በጀልባው ውስጥ የነበሩት፣ “በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብለው ሰገዱለት።

ፈውስ በጌንሴሬጥ

34ባሕሩን ከተሻገሩ በኋላ ጌንሴሬጥ ወደ ተባለ ቦታ ደረሱ። 35ነዋሪዎቹም ኢየሱስ መሆኑን ባወቁ ጊዜ፣ በዙሪያው ወዳለ አካባቢ ሁሉ መልእክት ላኩ፤ የታመሙትን ሁሉ ወደ እርሱ በማስመጣት፣ 36በሽተኞቹ የልብሱን ጫፍ ብቻ ይነኩ ዘንድ እንዲፈቅድላቸው ለመኑት፤ የነኩትም ሁሉ ተፈወሱ።

New International Reader’s Version

Matthew 14:1-36

John the Baptist’s Head Is Cut Off

1At that time Herod, the ruler of Galilee and Perea, heard reports about Jesus. 2He said to his attendants, “This is John the Baptist. He has risen from the dead! That is why he has the power to do miracles.”

3Herod had arrested John. He had tied him up and put him in prison because of Herodias. She was the wife of Herod’s brother Philip. 4John had been saying to Herod, “It is against the Law for you to have her as your wife.” 5Herod wanted to kill John. But he was afraid of the people, because they thought John was a prophet.

6On Herod’s birthday the daughter of Herodias danced for Herod and his guests. She pleased Herod very much. 7So he promised to give her anything she asked for. 8Her mother told her what to say. So the girl said to Herod, “Give me the head of John the Baptist on a big plate.” 9The king was very upset. But he thought of his promise and his dinner guests. So he told one of his men to give her what she asked for. 10Herod had John’s head cut off in the prison. 11His head was brought in on a big plate and given to the girl. She then carried it to her mother. 12John’s disciples came and took his body and buried it. Then they went and told Jesus.

Jesus Feeds Five Thousand

13Jesus heard what had happened to John. He wanted to be alone. So he went in a boat to a quiet place. The crowds heard about this. They followed him on foot from the towns. 14When Jesus came ashore, he saw a large crowd. He felt deep concern for them. He healed their sick people.

15When it was almost evening, the disciples came to him. “There is nothing here,” they said. “It’s already getting late. Send the crowds away. They can go and buy some food in the villages.”

16Jesus replied, “They don’t need to go away. You give them something to eat.”

17“We have only five loaves of bread and two fish,” they answered.

18“Bring them here to me,” he said. 19Then Jesus directed the people to sit down on the grass. He took the five loaves and the two fish. He looked up to heaven and gave thanks. He broke the loaves into pieces. Then he gave them to the disciples. And the disciples gave them to the people. 20All of them ate and were satisfied. The disciples picked up 12 baskets of leftover pieces. 21The number of men who ate was about 5,000. Women and children also ate.

Jesus Walks on the Water

22Right away Jesus made the disciples get into the boat. He had them go on ahead of him to the other side of the Sea of Galilee. Then he sent the crowd away. 23After he had sent them away, he went up on a mountainside by himself to pray. Later that night, he was there alone. 24The boat was already a long way from land. It was being pounded by the waves because the wind was blowing against it.

25Shortly before dawn, Jesus went out to the disciples. He walked on the lake. 26They saw him walking on the lake and were terrified. “It’s a ghost!” they said. And they cried out in fear.

27Right away Jesus called out to them, “Be brave! It is I. Don’t be afraid.”

28“Lord, is it you?” Peter asked. “If it is, tell me to come to you on the water.”

29“Come,” Jesus said.

So Peter got out of the boat. He walked on the water toward Jesus. 30But when Peter saw the wind, he was afraid. He began to sink. He cried out, “Lord! Save me!”

31Right away Jesus reached out his hand and caught him. “Your faith is so small!” he said. “Why did you doubt me?”

32When they climbed into the boat, the wind died down. 33Then those in the boat worshiped Jesus. They said, “You really are the Son of God!”

34They crossed over the lake and landed at Gennesaret. 35The men who lived there recognized Jesus. So they sent a message all over the nearby countryside. People brought all those who were sick to Jesus. 36They begged him to let those who were sick just touch the edge of his clothes. And all who touched his clothes were healed.