ማቴዎስ 13 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 13:1-58

የዘሪው ምሳሌ

13፥1-15 ተጓ ምብ – ማር 4፥1-12ሉቃ 8፥4-10

13፥1617 ተጓ ምብ – ሉቃ 10፥2324

13፥18-23 ተጓ ምብ – ማር 4፥13-20ሉቃ 8፥11-15

1በዚያኑ ቀን ኢየሱስ ከቤት ወጥቶ በባሕሩ አጠገብ ተቀመጠ። 2ብዙ ሕዝብም ስለ ከበበው በባሕሩ ዳር ትቷቸው ጀልባ ላይ ወጥቶ ተቀመጠ። 3ብዙ ነገሮችን በምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፤ “አንድ ገበሬ ዘር ሊዘራ ወጣ። 4ሲዘራም ሳለ፣ አንዳንዱ ዘር መንገድ ዳር ወደቀ፤ ወፎችም መጥተው ለቅመው በሉት። 5አንዳንዱ ዘር ዐፈሩ ስስ በሆነ፣ ድንጋያማ መሬት ላይ ወደቀ፤ ዐፈሩ ስስ ስለ ሆነም ፈጥኖ በቀለ። 6ነገር ግን ፀሓይ ሲመታው ጠወለገ፤ ሥር ባለ መስደዱም ደረቀ። 7አንዳንዱም ዘር በእሾኽ መካከል ወደቀ፤ እሾኹም አደገና ቡቃያውን ዐንቆ አስቀረው፤ 8ሌላው ዘር ደግሞ በጥሩ መሬት ላይ ወደቀ፤ ፍሬም አፈራ፤ አንዱ መቶ፣ አንዱ ስድሳ፣ አንዱም ሠላሳ ፍሬ ሰጠ። 9ሰሚ ጆሮ ያለው ይስማ!”

10ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው፣ “ለምን ለሕዝቡ በምሳሌ ትናገራለህ?” አሉት።

11እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ለእናንተ የመንግሥተ ሰማይን ምስጢር ማወቅ ተሰጥቷችኋል፤ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም። 12ላለው ይጨመርለታል፤ ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያ ያለው እንኳ ይወሰድበታል። 13ስለዚህ እንዲህ በማለት በምሳሌ የምነግራቸው ለዚህ ነው፤

“እያዩ፣ አያዩም፤

እየሰሙ፣ አይሰሙም ወይም አያስተውሉም፤

14እንዲህ ተብሎ የተነገረው የኢሳይያስ ትንቢት በእነርሱ ይፈጸማል፤

“ ‘መስማትንስ ትሰማላችሁ፤ ነገር ግን አታስተውሉም፤

ማየትንም ታያላችሁ፤ ነገር ግን ልብ አትሉም።

15የሕዝቡ ልብ ደንድኗልና፤

ጆሯቸውም አይሰማም፤

እንዳያዩም ዐይናቸውን ጨፍነዋል፤

ይህ ባይሆን ኖሮ፣ በዐይናቸው አይተው፣

በጆሯቸው ሰምተው፣

በልባቸውም አስተውለው፣

ወደ እኔ በተመለሱና በፈወስኋቸው ነበር።’

16የእናንተ ዐይኖች ስለሚያዩ፣ ጆሮዎቻችሁም ስለሚሰሙ ግን የተባረኩ ናቸው። 17እውነት እላችኋለሁ፤ ብዙ ነቢያትና ብዙ ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ለማየትና የምትሰሙትንም ለመስማት ተመኝተው ነበር፤ ግን አልሆነላቸውም።

18“እንግዲህ የዘሪውን ምሳሌ ስሙ፤ 19የእግዚአብሔርን መንግሥት ቃል ሰምቶ ከማያስተውል ከማንኛውም ሰው ልብ ውስጥ ክፉው መጥቶ የተዘራውን ዘር ይነጥቃል። ይህ እንግዲህ በመንገድ ዳር የተዘራው ዘር ነው። 20በድንጋያማ መሬት ላይ የተዘራው፣ ቃሉን ሰምቶ ወዲያውኑ በደስታ የሚቀበለውን ሰው ይመስላል። 21ነገር ግን ሥር መስደድ ባለ መቻሉ ብዙ አይቈይም፤ በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት ሲመጣ ወዲያውኑ ይሰናከላል። 22በእሾኽ መካከል የተዘራው ዘር ቃሉን ሰምቶ ለዚህ ዓለም በመጨነቅና በብልጽግና ሐሳብ በመታለል ታንቆ ያላፈራን ሰው ይመስላል። 23በጥሩ መሬት ላይ የተዘራው ዘር ግን ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውለውን ሰው ይመስላል፤ በርግጥም ፍሬ ያፈራል፤ አንዱ መቶ፣ አንዱ ስድሳ፣ አንዱም ሠላሳ ፍሬ ሰጠ።”

የእንክርዳዱ ምሳሌ

24ኢየሱስም ሌላ ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፤ “መንግሥተ ሰማይ በዕርሻው ቦታ ጥሩ ዘር የዘራን ሰው ትመስላለች። 25ነገር ግን ሰው ሁሉ ተኝቶ ሳለ፣ ጠላቱ መጥቶ በስንዴው መካከል እንክርዳድ ዘርቶ ሄደ። 26ስንዴው በቅሎ ማፍራት ሲጀምር እንክርዳዱም አብሮ ብቅ አለ።

27“የዕርሻው ባለቤት አገልጋዮችም ወደ እርሱ ቀርበው፣ ‘ጌታ ሆይ፤ በዕርሻህ ቦታ ጥሩ ዘር ዘርተህ አልነበረምን? እንክርዳዱ ከየት መጣ?’ አሉት።

28“እርሱም፣ ‘የጠላት ሥራ ነው’ አላቸው።

“አገልጋዮቹም፣ ‘እንክርዳዱን ሄደን እንድንነቅለው ትፈልጋለህ?’ ብለው ጠየቁት።

29“እርሱ ግን፣ ‘አይሆንም፤ ምክንያቱም እንክርዳዱን እንነቅላለን ስትሉ ስንዴውንም አብራችሁ ልትነቅሉ ትችላላችሁ፤ 30ተዉአቸው፤ እስከ መከር ጊዜ አብረው ይደጉ። በዚያን ጊዜ ዐጫጆቹን እንክርዳዱን አስቀድማችሁ ንቀሉ፤ በእሳትም እንዲቃጠል በየነዶው እሰሩት፤ ስንዴውን ግን ሰብስባችሁ በጐተራዬ ክተቱ እላቸዋለሁ’ አላቸው።”

የሰናፍጭና የእርሾ ምሳሌ

13፥31-32 ተጓ ምብ – ማር 4፥30-32

13፥31-33 ተጓ ምብ – ሉቃ 13፥18-21

31ሌላ ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፤ “መንግሥተ ሰማይ አንድ ሰው ወስዶ በዕርሻው ቦታ የዘራትን የሰናፍጭ ዘር ትመስላለች። 32የሰናፍጭ ዘር ከሌሎች ዘሮች ሁሉ ያነሰች ብትሆንም፣ ስታድግ ግን ከቍጥቋጦዎች ሁሉ በልጣ፣ የሰማይ ወፎች መጥተው በቅርንጫፎቿ ላይ እስኪያርፉ ድረስ ዛፍ ትሆናለች።”

33አሁንም ሌላ ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፤ “መንግሥተ ሰማይ ሴት ወስዳ ሊጡ በሙሉ እስኪቦካ ድረስ በሦስት መስፈሪያ13፥33 ምናልባት 22 ሊትር ያህል ዱቄት ውስጥ በመደባለቅ የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች።”

34ኢየሱስ ለሕዝቡ ይህን ሁሉ በምሳሌ ተናገረ፤ ምሳሌም ሳይጠቀም የነገራቸው አንድም ነገር አልነበረም። 35በዚህም በነቢዩ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ተፈጸመ፤

“አፌን በምሳሌ እከፍታለሁ፤

ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተሰወረውንም እናገራለሁ።”

የእንክርዳዱ ምሳሌ ትርጕም

36ከዚያም ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው፣ “በዕርሻው ውስጥ ስላለው እንክርዳድ የተናገርኸውን ምሳሌ ትርጕም ንገረን” አሉት።

37እርሱም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ጥሩውን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው፤ 38ዕርሻውም ይህ ዓለም ነው፤ ጥሩው ዘር የእግዚአብሔርን መንግሥት ልጆች ያመለክታል፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፤ 39ዘርቶት የሄደው ጠላትም ዲያብሎስ ነው፤ መከሩ የዓለም መጨረሻ ሲሆን፣ ዐጫጆቹም መላእክት ናቸው።

40“እንክርዳዱ ተነቅሎ በእሳት እንደሚቃጠል ሁሉ በዓለም መጨረሻም እንዲሁ ይሆናል። 41የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፤ እነርሱም ለኀጢአት ምክንያት የሆኑትንና ክፉ የሚያደርጉትን ሁሉ ለቅመው ከመንግሥቱ ያወጣሉ። 42ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ወደ እቶን እሳት ይጥሏቸዋል። 43በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሓይ ያበራሉ። ሰሚ ጆሮ ያለው ይስማ።

የተደበቀ ሀብትና የዕንቍው ምሳሌ

44“መንግሥተ ሰማይ በዕርሻ ውስጥ የተደበቀ ሀብት ትመስላለች፤ አንድ ሰው ባገኛት ጊዜ መልሶ ሸሸጋት፤ ከመደሰቱም የተነሣ፣ ሄዶ ያለውን ሁሉ በመሸጥ ያንን የዕርሻ ቦታ ገዛ።

45“እንዲሁም መንግሥተ ሰማይ ውብ ዕንየሚፈልግ ነጋዴ ትመስላለች፤ 46እጅግ ውድ የሆነ ዕንባገኘም ጊዜ፣ ሄዶ ያለውን ሁሉ ሸጦ ገዛው።

የመረቡ ምሳሌ

47“ደግሞም መንግሥተ ሰማይ ወደ ባሕር ተጥሎ የዓሣ ዐይነቶችን የያዘ መረብ ትመስላለች፤ 48ዓሣ አጥማጆቹ መረቡ ሲሞላላቸው ጐትተው ወደ ባሕሩ ዳር አወጡት፤ ከዚያም ተቀምጠው ጥሩ ጥሩውን እየለዩ በቅርጫት ውስጥ ጨመሩ፤ መጥፎ መጥፎውን ግን ጣሉት። 49በዓለም መጨረሻም ልክ እንደዚሁ ይሆናል፤ መላእክት መጥተው ኀጢአተኞችን ከጻድቃን በመለየት፣ 50ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ወደ እቶን እሳት ይጥሏቸዋል።”

51ኢየሱስ፣ “ይህ ሁሉ ገብቷችኋል?” አላቸው።

እነርሱም፣ “አዎን” አሉት።

52እርሱም፣ “ስለዚህም የመንግሥተ ሰማይን ምስጢር የተረዳ ማንኛውም የኦሪት ሕግ መምህር፣ ከከበረ ሀብቱ ክምችት አዲሱንም አሮጌውንም የሚያወጣ ባለ ንብረት ይመስላል” አላቸው።

በገዛ አገሩ ያልተከበረው ነቢይ

13፥54-58 ተጓ ምብ – ማር 6፥1-6

53ኢየሱስ እነዚህን ምሳሌዎች እንደ ጨረሰ፣ ከዚያ ስፍራ ተነሥቶ ሄደ፤ 54ወደ ገዛ አገሩ መጣ፤ በምኵራባቸውም ሕዝቡን ያስተምር ጀመር። እነርሱም በመገረም እንዲህ አሉ፤ “ይህ ሰው ይህን ጥበብና እነዚህን ታምራት የማድረግ ኀይል ከየት አገኘ? 55ይህ የዐናጢው ልጅ አይደለምን? የእናቱስ ስም ማርያም አይደለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብ፣ ዮሴፍ፣ ስምዖንና ይሁዳ አይደሉምን? 56እኅቶቹስ ከእኛው ጋር አይደሉምን? ታዲያ ይህ ሰው ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው?” 57ስለዚህም ሳይቀበሉት ቀሩ።

ኢየሱስ ግን፣ “ነቢይ የማይከበረው በራሱ አገርና በራሱ ቤት ብቻ ነው” አላቸው። 58ባለ ማመናቸውም ምክንያት ብዙ ታምራትን በዚያ አላደረገም።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מתי 13:1-58

1באותו יום, בשעה מאוחרת יותר, עזב ישוע את הבית וירד אל החוף. 2תוך זמן קצר התאסף שם קהל כה רב, עד שישוע נאלץ להיכנס לסירה, ואילו כל העם נשאר על החוף. 3ישוע הרבה ללמד את העם במשלים, והנה אחד מהם:

”איכר יצא לזרוע בשדה. 4כשפיזר את הזרעים נפלו אחדים מהם בצד הדרך, והציפורים באו ואכלו אותם. 5זרעים אחדים נפלו על אדמה סַלעִית, במקום שבו לא הייתה אדמה רבה. הנבטים צמחו במהירות באדמה הרדודה, 6אולם השמש הלוהטת צרבה אותם והם התייבשו ומתו, כי השורשים לא היו עמוקים. 7זרעים אחדים נפלו בין הקוצים, ואלה חנקו את הצמחים הרכים. 8אולם זרעים אחדים נפלו על אדמה טובה ופורייה, ונשאו פרי מבורך ורב פי שלושים, פי שישים ואפילו פי מאה. 9מי שמסוגל לשמוע, שיקשיב!“

10תלמידיו של ישוע באו אליו ושאלו: ”מדוע אתה משתמש תמיד בדוגמאות קשות כל כך?“

11הסביר להם ישוע: ”רק לכם מותר לדעת את סודות מלכות השמים; לאחרים לא ניתן לדעת אותם. 12כי מי שיש לו – יינתן לו עוד ויהיה לו שפע רב; ומי שאין – גם המעט שיש לו יילקח ממנו. 13אני מדבר אל בני אדם במשלים מכיוון שכאשר מראים להם משהו הם לא רואים, וכאשר אומרים להם משהו הם לא שומעים וגם לא מבינים. 14כך התקיימה נבואתו של ישעיהו:13‏.14 יג 14 ישעיהו ו 9‏-10

’שמעו שמוע ואל תבינו,

וראו ראו ואל תדעו.

15כי השמן לב העם הזה

ואזניו הכבד ועיניו השע,

פן יראה בעיניו ובאזניו ישמע,

ולבבו יבין ושב ורפא לו‘.

16”אולם אשרי עיניכם כי הן רואות, ואשרי אוזניכם כי הן שומעות. 17הרבה נביאים וצדיקים השתוקקו לראות את מה שאתם רואים ולשמוע את מה שאתם שומעים, אך לא זכו.

18”זהו פירוש המשל: 19השביל הקשה שעליו נפלו חלק מהזרעים מסמל את לבו של האדם השומע את הבשורה, אך אינו מבין אותה; ואז בא השטן וחוטף את מה שנזרע בלבו. 20האדמה הסלעית מסמלת את לבו של האדם השומע את הבשורה ומקבל אותה בשמחה. 21אולם לאמונתו אין עומק, והזרעים אינם מכים שורשים עמוקים. משום כך, ברגע של קושי ומבחן נעלמת התלהבותו והוא נובל. 22האדמה המכוסה קוצים מסמלת את האדם ששמע את הבשורה, אולם דאגות החיים ורצונו להתעשר חונקים את דבר האלוהים, והוא הולך ומפחית בעבודת אלוהים. 23האדמה הטובה מסמלת את לבו של אדם המקשיב לבשורה, מבין אותה ומביא פרי רב, פי מאה, פי שישים ופי שלושים ממה שנזרע בלבם.“

24ישוע סיפר להם משל נוסף: ”מלכות השמים דומה לאיכר שזרע בשדה שלו זרעים טובים. 25אולם לילה אחד, בזמן שהאיכר ישן, בא אויבו וזרע עשבי בר13‏.25 יג 25 זונין בין החיטה. 26כשהחלה החיטה לנבוט, נבטו גם עשבי הבר.

27”משרתיו של האיכר באו אליו ואמרו: ’אדוננו, השדה שבו זרעת זרעים משובחים מלא עשבים!‘

28” ’אחד מאויבי עשה זאת‘, אמר האיכר.

” ’האם אתה רוצה שנעקור את העשבים השוטים?‘ שאלו המשרתים.

29” ’לא‘, השיב האיכר. ’אתם עלולים לעקור בטעות גם את החיטה. 30הניחו להם לגדול יחד עד הקציר, ואז אומר לקוצרים לאסוף תחילה את העשבים השוטים ולשרוף אותם, ולאחר מכן לאסוף את החיטה ולהכניסה לאסם‘. “

31‏-32ישוע סיפר להם עוד משל: ”מלכות השמים דומה לגרגר זעיר של צמח החרדל אשר נזרע בשדה. למרות שגרגר זה קטן ביותר, הוא גדל להיות אחד הצמחים הגדולים ביותר, והציפורים יכולות לבנות להן קן בין ענפיו.“

33ישוע נתן להם דוגמה נוספת: ”אפשר להמשיל את מלכות השמים לאישה המתכוננת לאפות לחם. היא לוקחת את כמות הקמח הדרושה ושמה מעט שמרים, עד שהבצק כולו תופח.“

34את כל אלה דיבר ישוע אל הקהל במשלים; ובלי משל לא דיבר אליהם. 35כך הוא קיים את הנבואה:13‏.35 יג 35 תהלים עח 2 ”אפתחה במשל פי, אביעה חידות מני־קדם“.

36לאחר מכן עזב ישוע את ההמון ונכנס הביתה. תלמידיו ביקשו ממנו שיסביר להם את משל העשבים בשדה החיטה.

37”בן־האדם הוא האיכר הזורע את הזרעים הטובים“, הסביר להם ישוע. 38”השדה מסמל את העולם, הזרעים מסמלים את בני מלכות האלוהים, והעשבים מסמלים את האנשים השייכים לשטן. 39האויב שזרע את עשבי־הבר בשדה החיטה הוא השטן, הקציר הוא סוף העולם והקוצרים הם המלאכים.“

40”כשם שבמשל זה נאספו העשבים ונשרפו, כך יהיה גם בסוף העולם. 41בן־האדם ישלח את מלאכיו, והם ידרשו מתוך המלכות את כל עושי הרע ואת כל אלה שמכשילים את האחרים, 42וישליכו אותם לכבשן שישרוף אותם. שם הם יבכו ויחרקו שיניים 43ואילו הצדיקים יזרחו כשמש במלכות אביהם. מי שמסוגל לשמוע, שיקשיב!

44”מלכות השמים דומה לאוצר שאיש גילה בתוך שדה. בהתלהבותו הרבה מכר האיש את כל אשר היה לו, כדי שיוכל לקנות את השדה עם האוצר שמצא בו.“

45”מלכות השמים דומה לפנינה נהדרת שמצא סוחר בעת שחיפש פנינים מובחרות. 46כשגילה הסוחר את הפנינה היקרה, שהייתה ממש ’מציאה‘, הלך ומכר את כל רכושו, כדי שיוכל לקנות אותה.“

47”אפשר לתאר את מלכות השמים גם בסיפור על דייג שהשליך את רשתו לים, ונלכדו בה כל מיני דגים. 48כשנמלאה הרשת, הדייג הוציא אותה אל החוף והחל למיין את הדגים: את הטובים שם בסלים, ואת האחרים השליך. 49כך יהיה גם בסוף העולם: המלאכים יבואו ויפרידו בין הרשעים ובין הצדיקים. 50את הרשעים ישליכו המלאכים לאש – שם הם יבכו ויחרקו שיניים.“

51”האם אתם מבינים?“ שאל אותם ישוע.

”כן,“ ענו התלמידים, ”אנחנו מבינים.“

52וישוע הוסיף: ”תלמיד שלמד והבין את מלכות השמים דומה לאיש עשיר שמוציא מאוצרו דברים עתיקים וגם חדשים.“

53כשסיים ישוע לספר להם את המשלים האלה, המשיך בדרכו. 54כשהגיע אל ביתו (בנצרת שבגליל) לימד את האנשים בבתי־הכנסת, והפליא את כולם בחכמתו ובניסים.

55”כיצד ייתכן הדבר?“ תמהו האנשים. ”הלא הוא בנו של הנגר, ואנחנו מכירים את מרים אמו ואת אחיו – יעקב, יוסף, שמעון ויהודה! 56גם את אחיותיו אנחנו מכירים – הרי כולן גרות כאן. כיצד הוא יכול להיות גדול כל כך?“ 57והם רגזו מאוד על ישוע.

”אין נביא בעירו!“ אמר להם ישוע. ”את הנביא מכבדים בכל מקום, מלבד בביתו ובקרב בני־עמו.“ 58ומאחר שלא האמינו בו הוא חולל שם נסים מעטים בלבד.