ማርቆስ 5 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 5:1-43

አጋንንት ያደሩበት ሰው መፈወሱ

5፥1-17 ተጓ ምብ – ማቴ 8፥28-34ሉቃ 8፥26-37

5፥18-20 ተጓ ምብ – ሉቃ 8፥3839

1ባሕሩን ተሻግረው ጌራሴኖን5፥1 አንዳንድ ቅጆች ደግሞ ጌርጌሴኖን ይላሉ። ወደ ተባለ አገር መጡ። 2ኢየሱስ ከጀልባ እንደ ወረደ፣ ርኩስ5፥2 ወይም ክፉ፤ እንዲሁም 8 እና 13 ይመ መንፈስ ያደረበት ሰው ከመቃብር ቦታ ወጥቶ ሊገናኘው ወደ እርሱ መጣ። 3ይህ ሰው በመቃብር ቦታ ውስጥ የሚኖርና ማንም በሰንሰለት እንኳ ሊያስረው የማይችል ነበር። 4ብዙ ጊዜ በእግር ብረትና በሰንሰለት ይታሰር ነበር፤ ነገር ግን የእጅ ሰንሰለቱን ይበጥስ፣ የእግር ብረቱንም ይሰብር ነበር። ማንም ይዞ ሊያቈየው የሚችል አልነበረም።

5በመቃብሮቹና በተራራዎቹ መካከል ቀንና ሌሊት እየተዘዋወረ በመጮኽ ሰውነቱን በድንጋይ ይቈራርጥ ነበር።

6ይህም ሰው ኢየሱስን ከሩቅ ባየው ጊዜ ወደ እርሱ ሮጦ ከፊቱ ተንበርክኮ ሰገደለት፤ 7በታላቅ ድምፅ ጮኾም፣ “አንተ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፤ ከእኔ ምን አለህ? እንዳታሠቃየኝ በእግዚአብሔር ይዤሃለሁ” አለው። 8ይህንም ያለው ኢየሱስ፣ “አንተ ርኩስ መንፈስ ከዚህ ሰው ውጣ!” ብሎት ስለ ነበር ነው።

9ከዚያም ኢየሱስ፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው።

“ብዙ ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው” አለው። 10ከአገር እንዳያስወጣቸውም አጥብቆ ለመነው።

11በአቅራቢያውም በሚገኝ ኰረብታ ላይ ትልቅ የዐሣማ መንጋ ተሰማርቶ ነበር። 12ርኩሳን መናፍስቱም ኢየሱስን፣ “ወደ ዐሣማዎቹ ስደደን፤ እንድንገባባቸውም ፍቀድልን” ብለው ለመኑት። 13እርሱም ፈቀደላቸው። ርኩሳን መናፍስቱም ወጥተው በዐሣማዎቹ ገቡባቸው፤ ሁለት ሺሕ ያህል ዐሣማዎችም በገደሉ አፋፍ በመንደርደር ቍልቍል ወርደው በባሕር ውስጥ ሰጠሙ።

14እረኞቹ ሸሽተው ሄዱ፤ ወሬውን በከተማና በገጠር አዳረሱት፤ ሕዝቡም የሆነውን ለማየት ካለበት ወጣ። 15ወደ ኢየሱስም በመጡ ጊዜ፣ የአጋንንት ሰራዊት ዐድረውበት የነበረው ሰው፣ ልብስ ለብሶና አእምሮው ተመልሶለት በዚያ ተቀምጦ አዩት፤ ፈሩም። 16ይህን ያዩ ሰዎችም አጋንንት ስላደረበት ሰው የተደረገውንና ስለ ዐሣማዎቹም ለሕዝቡ አወሩ። 17ከዚያም ሕዝቡ አገራቸውን ለቅቆ እንዲሄድላቸው ኢየሱስን ይለምኑት ጀመር።

18ኢየሱስ ወደ ጀልባዪቱ በሚገባበት ጊዜ፣ አጋንንት ዐድሮበት የነበረው ሰው አብሮት ለመሄድ ለመነው። 19ኢየሱስ አልፈቀደለትም፤ ነገር ግን፣ “ወደ ቤትህ ሂድ፣ ለዘመዶችህም ጌታ ምን ያህል ታላቅ ነገር እንዳደረገልህና ያሳየህን ምሕረት ንገራቸው” አለው። 20ሰውየውም ሄደ፤ ኢየሱስ ያደረገለትን ነገር ሁሉ ዐሥር ከተማ5፥20 ዐሥር ከተማ የሚባለውን አካባቢ ግሪኩ ዴካፖሊስ ይለዋል። በተባለው አገር ያወራ ጀመር፤ የሰሙትም ሁሉ ተደነቁ።

የሞተችው ልጅና የታመመችው ሴት

5፥22-43 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥18-26ሉቃ 8፥41-56

21ኢየሱስ እንደ ገና በጀልባ ወደ ማዶ በተሻገረ ጊዜ፣ ብዙ ሕዝብ በዙሪያው ተሰባሰበ፤ በባሕሩ ዳርቻም እንዳለ፣ 22ከምኵራብ አለቆች አንዱ ኢያኢሮስ የተባለው ወደዚያ መጥቶ ስለ ነበር፣ ኢየሱስን ባየው ጊዜ በእግሩ ላይ ወድቆ፣ 23“ትንሿ ልጄ በሞት አፋፍ ላይ ናትና ድና በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ጫንባት” በማለት አጥብቆ ለመነው። 24ኢየሱስም አብሮት ሄደ።

ብዙ ሕዝብም ዙሪያውን እያጨናነቀው ተከተለው። 25ዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈስሳት የኖረችም ሴት በዚያ ነበረች፤ 26በብዙ ባለ መድኀኒቶች ዘንድ በመንከራተት ያላትን ሁሉ ብትጨርስም፣ ሕመሙ ባሰባት እንጂ አልተሻላትም ነበር። 27ስለ ኢየሱስም በሰማች ጊዜ፣ ከበስተ ኋላው በሰዎች መካከል መጥታ ልብሱን ነካች፤ 28ምክንያቱም፣ “እንደ ምንም ብዬ ልብሱን ብቻ እንኳ ብነካ እፈወሳለሁ” የሚል እምነት ነበራት። 29የሚፈስሰው ደሟ ወዲያውኑ ቆመ፤ ከሥቃይዋ መገላገሏም በሰውነቷ ታወቃት።

30ወዲያውኑ ኢየሱስ፣ ኀይል ከእርሱ እንደ ወጣ ዐውቆ፤ ወደ ሕዝቡ ዘወር በማለት፣ “ልብሴን የነካው ማን ነው?” አለ።

31ደቀ መዛሙርቱም፣ “ሕዝቡ ተጨናንቆ ሲጋፋህ እያየህ፣ ‘ማን ነው የነካኝ?’ እንዴት ትላለህ?” አሉት።

32ኢየሱስ ግን ይህን ያደረገው ማን እንደ ሆነ ለማየት ዙሪያውን ተመለከተ። 33ሴትዮዋም ምን እንደ ተደረገላት ባወቀች ጊዜ እየፈራችና እየተንቀጠቀጠች መጥታ በፊቱ ተደፋች፤ እውነቱንም ሁሉ ነገረችው። 34እርሱም፣ “ልጄ ሆይ፤ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ፤ ከሥቃይሽም ዕረፊ” አላት።

35ኢየሱስም በመነጋገር ላይ እያለ፣ ሰዎች ከምኵራቡ አለቃ ከኢያኢሮስ ቤት መጥተው፣ “ልጅህ ሞታለች፤ ከእንግዲህ መምህሩን ለምን ታደክመዋለህ?” አሉት።

36ኢየሱስ ግን ሰዎቹ የተናገሩትን ችላ በማለት የምኵራቡን አለቃ፣ “እመን ብቻ እንጂ አትፍራ፤” አለው።

37ከጴጥሮስና ከያዕቆብ እንዲሁም ከያዕቆብ ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም። 38ወደ ምኵራቡ አለቃ ቤት እንደ ደረሱ፣ ኢየሱስ ግርግሩንና ሰዎቹም ዋይ ዋይ እያሉ አምርረው ሲያለቅሱ ተመለከተ። 39ወደ ቤትም ገብቶ፣ “ይህ ሁሉ ግርግርና ልቅሶ ምንድን ነው? ብላቴናዪቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” አላቸው። 40ሰዎቹ ግን ሣቁበት።

ሰዎቹን ሁሉ ከቤት ካስወጣ በኋላ፣ የብላቴናዪቱን አባትና እናት እንዲሁም አብረውት የመጡትን ደቀ መዛሙርት አስከትሎ ብላቴናዪቱ ወዳለችበት ገባ። 41ከዚያም የብላቴናዪቱን እጅ ይዞ፣ “ጣሊታ ቁሚ!” አላት፤ ትርጕሙም፣ “አንቺ ልጅ ተነሺ” ማለት ነው። 42ብላቴናዪቱም ወዲያውኑ ተነሥታ ቆመች፤ ወዲያ ወዲህም ሄደች። ዕድሜዋም ዐሥራ ሁለት ዓመት ነበር። ሰዎቹም በሁኔታው እጅግ ተደነቁ። 43እርሱም ይህን ነገር ማንም እንዳያውቅ አጥብቆ አስጠነቀቃቸው፤ የሚበላ ነገር እንዲሰጧትም ነገራቸው።

New International Reader’s Version

Mark 5:1-43

Jesus Heals a Man Controlled by Demons

1They went across the Sea of Galilee to the area of the Gerasenes. 2Jesus got out of the boat. A man controlled by an evil spirit came from the tombs to meet him. 3The man lived in the tombs. No one could keep him tied up anymore. Not even a chain could hold him. 4His hands and feet had often been chained. But he tore the chains apart. And he broke the iron cuffs on his ankles. No one was strong enough to control him. 5Night and day he screamed among the tombs and in the hills. He cut himself with stones.

6When he saw Jesus a long way off, he ran to him. He fell on his knees in front of him. 7He shouted at the top of his voice, “Jesus, Son of the Most High God, what do you want with me? Swear to God that you won’t hurt me!” 8This was because Jesus had said to him, “Come out of this man, you evil spirit!”

9Then Jesus asked the demon, “What is your name?”

“My name is Legion,” he replied. “There are many of us.” 10And he begged Jesus again and again not to send them out of the area.

11A large herd of pigs was feeding on the nearby hillside. 12The demons begged Jesus, “Send us among the pigs. Let us go into them.” 13Jesus allowed it. The evil spirits came out of the man and went into the pigs. There were about 2,000 pigs in the herd. The whole herd rushed down the steep bank. They ran into the lake and drowned.

14Those who were tending the pigs ran off. They told the people in the town and countryside what had happened. The people went out to see for themselves. 15Then they came to Jesus. They saw the man who had been controlled by many demons. He was sitting there. He was now dressed and thinking clearly. All this made the people afraid. 16Those who had seen it told them what had happened to the man. They told about the pigs as well. 17Then the people began to beg Jesus to leave their area.

18Jesus was getting into the boat. The man who had been controlled by demons begged to go with him. 19Jesus did not let him. He said, “Go home to your own people. Tell them how much the Lord has done for you. Tell them how kind he has been to you.” 20So the man went away. In the area known as the Ten Cities, he began to tell how much Jesus had done for him. And all the people were amazed.

Jesus Heals a Dead Girl and a Suffering Woman

21Jesus went across the Sea of Galilee in a boat. It landed at the other side. There a large crowd gathered around him. 22Then a man named Jairus came. He was a synagogue leader. When he saw Jesus, he fell at his feet. 23He begged Jesus, “Please come. My little daughter is dying. Place your hands on her to heal her. Then she will live.” 24So Jesus went with him.

A large group of people followed. They crowded around him. 25A woman was there who had a sickness that made her bleed. It had lasted for 12 years. 26She had suffered a great deal, even though she had gone to many doctors. She had spent all the money she had. But she was getting worse, not better. 27Then she heard about Jesus. She came up behind him in the crowd and touched his clothes. 28She thought, “I just need to touch his clothes. Then I will be healed.” 29Right away her bleeding stopped. She felt in her body that her suffering was over.

30At once Jesus knew that power had gone out from him. He turned around in the crowd. He asked, “Who touched my clothes?”

31“You see the people,” his disciples answered. “They are crowding against you. And you still ask, ‘Who touched me?’ ”

32But Jesus kept looking around. He wanted to see who had touched him. 33Then the woman came and fell at his feet. She knew what had happened to her. She was shaking with fear. But she told him the whole truth. 34He said to her, “Dear woman, your faith has healed you. Go in peace. You are free from your suffering.”

35While Jesus was still speaking, some people came from the house of Jairus. He was the synagogue leader. “Your daughter is dead,” they said. “Why bother the teacher anymore?”

36Jesus heard what they were saying. He told the synagogue leader, “Don’t be afraid. Just believe.”

37He let only Peter, James, and John, the brother of James, follow him. 38They came to the home of the synagogue leader. There Jesus saw a lot of confusion. People were crying and sobbing loudly. 39He went inside. Then he said to them, “Why all this confusion and sobbing? The child is not dead. She is only sleeping.” 40But they laughed at him.

He made them all go outside. He took only the child’s father and mother and the disciples who were with him. And he went in where the child was. 41He took her by the hand. Then he said to her, “Talitha koum!” This means, “Little girl, I say to you, get up!” 42The girl was 12 years old. Right away she stood up and began to walk around. They were totally amazed at this. 43Jesus gave strict orders not to let anyone know what had happened. And he told them to give her something to eat.