ማርቆስ 3 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 3:1-35

1በሌላ ጊዜ ወደ ምኵራብ ገባ፤ በዚያም እጁ የሰለለች ሰው ነበር። 2በምክንያት ሊከስሱት የሚፈልጉ ሰዎችም በሰንበት ቀን ይፈውሰው እንደ ሆነ ለማየት ይጠባበቁ ነበር። 3እርሱም እጁ የሰለለችውን ሰው፣ “በተሰበሰበው ሕዝብ ፊት ተነሥተህ ቁም” አለው።

4ኢየሱስም፣ “በሰንበት ቀን የተፈቀደው መልካም ማድረግ ነው ወይስ ክፉ? ሕይወት ማዳን ነውን ወይስ ማጥፋት?” አላቸው። እነርሱ ግን ዝም አሉ።

5በልባቸው ደንዳናነት ዐዝኖ በዙሪያው የቆሙትን በቍጣ ተመለከታቸውና ሰውየውን፣ “እጅህን ዘርጋ!” አለው፤ ሰውየውም እጁን ዘረጋ፤ እጁም ፍጹም ደኅና ሆነችለት።

6ፈሪሳውያንም እንዴት ሊያጠፉት እንደሚችሉ ከሄሮድስ ወገን ከሆኑት ጋር መመካከር ጀመሩ።

ብዙ ሰዎች ኢየሱስን ተከተሉ

3፥7-12 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥1516ሉቃ 6፥17-19

7ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ባሕሩ ሄደ፤ ከገሊላ የመጣ እጅግ ብዙ ሕዝብም ተከተለው፤ 8የሚሠራውን ነገር የሰሙ ሰዎችም ከይሁዳ፣ ከኢየሩሳሌም፣ ከኤዶምያስ፣ በዮርዳኖስ ማዶ ካለው አገር እንዲሁም ከጢሮስና ከሲዶና አካባቢ ወደ እርሱ መጡ። 9የተሰበሰበውም ሕዝብ እንዳያጨናንቀው አነስተኛ የሆነ ጀልባ እንዲያዘጋጁለት ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው። 10ብዙዎችን ፈውሶ ስለ ነበር፣ በሕመም የሚሠቃዩ ሁሉ ሊዳስሱት ይሽቀዳደሙ ነበር። 11ርኩሳን3፥11 ወይም ክፉ፤ እንዲሁም 30 ይመ መናፍስትም ባዩት ቍጥር ከፊቱ እየወደቁ፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ!” በማለት ይጮኹ ነበር። 12እርሱ ግን ማንነቱን እንዳይገልጹ አጥብቆ ይገሥጻቸው ነበር።

የዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት መሾም

3፥16-19 ተጓ ምብ – ማቴ 10፥2-4ሉቃ 6፥14-16ሐሥ 1፥13

13ኢየሱስ ወደ ተራራ ወጥቶ የሚፈልጋቸውን ወደ እርሱ እንዲመጡ ጠራቸው፤ እነርሱም ወደ እርሱ መጡ። 14ከእርሱ ጋር እንዲሆኑ፣ ለስብከትም ይልካቸው ዘንድ ዐሥራ ሁለቱን ሾማቸው፤ ሐዋርያትም ብሎ ጠራቸው3፥14 አንዳንድ ቅጆች ሐዋርያትም ብሎ ጠራቸው የሚለው ሐረግ የላቸውም።15አጋንንትን እንዲያስወጡም ሥልጣን ሰጣቸው። 16የሾማቸውም ዐሥራ ሁለቱ እነዚህ ናቸው፤ ጴጥሮስ ብሎ የጠራው ስምዖን፣ 17ቦአኔርጌስ ይኸውም፣ “የነጐድጓድ ልጆች” ብሎ የጠራቸው የዘብዴዎስ ልጆች ያዕቆብና ወንድሙ ዮሐንስ፤ 18እንድርያስ፣ ፊልጶስ፣ በርተሎሜዎስ፣ ማቴዎስ፣ ቶማስ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፣ ታዴዎስ፣ ተቀናቃኙ ስምዖን፣ 19እንዲሁም አሳልፎ የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ።

ኢየሱስና ብዔልዜቡል

3፥23-27 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥25-29ሉቃ 11፥17-22

20ከዚያም ኢየሱስ ወደ አንድ ቤት ገባ፤ እርሱና ደቀ መዛሙርቱ ምግብ መብላት እንኳ እስኪሳናቸው ድረስ ሕዝቡ እንደ ገና በብዛት ተሰበሰበ። 21ሁኔታውን የሰሙ ዘመዶቹም፣ “አእምሮውን ስቷል” በማለት ይዘውት ለመሄድ ወዳለበት መጡ።

22ከኢየሩሳሌም የመጡ ጸሐፍትም፣ “ብዔልዜቡል3፥22 ግሪኩ ብዔዜቡል ወይም ብዔልዜቡል ይላል። ዐድሮበታል፤ አጋንንትን የሚያወጣው በአጋንንት አለቃ ነው” አሉ።

23እርሱም ጠራቸውና በምሳሌ እንዲህ አላቸው፤ “ሰይጣን ሰይጣንን እንዴት ሊያስወጣ ይችላል? 24እርስ በርሱ የሚከፋፈል መንግሥት ሊጸና አይችልም፤ 25ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ሊቆም አይችልም። 26እንደዚሁም ሰይጣን እርስ በርሱ የሚፃረርና የሚከፋፈል ከሆነ ሊቆም አይችልም፤ ያበቃለታል። 27ከዚህም የተነሣ አንድ ሰው አስቀድሞ ኀይለኛውን ሰው ሳያስር ወደ ኀይለኛው ሰው ቤት ሊገባና ንብረቱን ሊዘርፍ አይችልም፤ ቤቱን መዝረፍ የሚቻለው ኀይለኛውን ሰው ሲያስር ብቻ ነው። 28እውነት እላችኋለሁ፤ የሰው ልጆች ኀጢአትና የሚሳደቡት ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል፤ 29ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል የሚናገር ሁሉ የዘላለም ኀጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም።”

30ይህንም ያለው፣ “ርኩስ መንፈስ አለበት” ስላሉት ነበር።

የኢየሱስ እናትና ወንድሞቹ

3፥31-35 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥46-50ሉቃ 8፥19-21

31ከዚህ በኋላ እናቱና ወንድሞቹ መጡ፤ በውጭ ቆመውም ሰው ልከውበት አስጠሩት። 32በዙሪያው የተቀመጡ ብዙ ሰዎችም፣ “እነሆ፤ እናትህና ወንድሞችህ ውጭ ይፈልጉሃል” አሉት።

33እርሱም መልሶ፣ “እናቴ ማን ናት፣ ወንድሞቼስ እነማን ናቸው?” አላቸው።

34በዙሪያው ወደ ተቀመጡትም በመመልከት፣ እንዲህ አለ፤ “እናቴና ወንድሞቼ እነዚህ ናቸው! 35የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ወንድሜ፣ እኅቴ፣ እናቴም ነውና።”

New International Version

Mark 3:1-35

Jesus Heals on the Sabbath

1Another time Jesus went into the synagogue, and a man with a shriveled hand was there. 2Some of them were looking for a reason to accuse Jesus, so they watched him closely to see if he would heal him on the Sabbath. 3Jesus said to the man with the shriveled hand, “Stand up in front of everyone.”

4Then Jesus asked them, “Which is lawful on the Sabbath: to do good or to do evil, to save life or to kill?” But they remained silent.

5He looked around at them in anger and, deeply distressed at their stubborn hearts, said to the man, “Stretch out your hand.” He stretched it out, and his hand was completely restored. 6Then the Pharisees went out and began to plot with the Herodians how they might kill Jesus.

Crowds Follow Jesus

7Jesus withdrew with his disciples to the lake, and a large crowd from Galilee followed. 8When they heard about all he was doing, many people came to him from Judea, Jerusalem, Idumea, and the regions across the Jordan and around Tyre and Sidon. 9Because of the crowd he told his disciples to have a small boat ready for him, to keep the people from crowding him. 10For he had healed many, so that those with diseases were pushing forward to touch him. 11Whenever the impure spirits saw him, they fell down before him and cried out, “You are the Son of God.” 12But he gave them strict orders not to tell others about him.

Jesus Appoints the Twelve

13Jesus went up on a mountainside and called to him those he wanted, and they came to him. 14He appointed twelve3:14 Some manuscripts twelve—designating them apostles— that they might be with him and that he might send them out to preach 15and to have authority to drive out demons. 16These are the twelve he appointed: Simon (to whom he gave the name Peter), 17James son of Zebedee and his brother John (to them he gave the name Boanerges, which means “sons of thunder”), 18Andrew, Philip, Bartholomew, Matthew, Thomas, James son of Alphaeus, Thaddaeus, Simon the Zealot 19and Judas Iscariot, who betrayed him.

Jesus Accused by His Family and by Teachers of the Law

20Then Jesus entered a house, and again a crowd gathered, so that he and his disciples were not even able to eat. 21When his family3:21 Or his associates heard about this, they went to take charge of him, for they said, “He is out of his mind.”

22And the teachers of the law who came down from Jerusalem said, “He is possessed by Beelzebul! By the prince of demons he is driving out demons.”

23So Jesus called them over to him and began to speak to them in parables: “How can Satan drive out Satan? 24If a kingdom is divided against itself, that kingdom cannot stand. 25If a house is divided against itself, that house cannot stand. 26And if Satan opposes himself and is divided, he cannot stand; his end has come. 27In fact, no one can enter a strong man’s house without first tying him up. Then he can plunder the strong man’s house. 28Truly I tell you, people can be forgiven all their sins and every slander they utter, 29but whoever blasphemes against the Holy Spirit will never be forgiven; they are guilty of an eternal sin.”

30He said this because they were saying, “He has an impure spirit.”

31Then Jesus’ mother and brothers arrived. Standing outside, they sent someone in to call him. 32A crowd was sitting around him, and they told him, “Your mother and brothers are outside looking for you.”

33“Who are my mother and my brothers?” he asked.

34Then he looked at those seated in a circle around him and said, “Here are my mother and my brothers! 35Whoever does God’s will is my brother and sister and mother.”