ማሕልየ መሓልይ 5 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 5:1-16

ሙሽራው

1እኅቴ ሙሽራዬ፣ ወደ አትክልት ቦታዬ መጥቻለሁ፤

ከርቤዬን ከቅመሜ ጋር ሰብስቤአለሁ፤

የማር እንጀራዬን ከነወለላው በልቻለሁ፤

ወይኔንና ወተቴንም ጠጥቻለሁ።

ባልንጀሮቿ

ወዳጆች ሆይ፤ ብሉ፤ ጠጡ፤

እናንት ፍቅረኞች ሆይ፤ እስክትረኩ ጠጡ።

ሙሽራዪቱ

2እኔ ተኝቻለሁ፤ ልቤ ግን ነቅቷል፤

ስሙ! ውዴ በር ያንኳኳል፤ እንዲህ ይላል፤

“እኅቴ ወዳጄ፣ ርግቤ፣

አንቺ እንከን የሌለብሽ፤ ክፈቺልኝ።

ራሴ በጤዛ፣

ጠጕሬም በሌሊቱ ርጥበት ረስርሷል።”

3ቀሚሴን አውልቄአለሁ፤

ታዲያ እንዴት እንደ ገና ልልበስ?

እግሬን ታጥቤአለሁ፤

እንዴት እንደ ገና ላቈሽሸው?

4ውዴ እጁን በበሩ ቀዳዳ አሾለከ፤

ልቤም ስለ እርሱ ይታወክ ጀመር።

5ለውዴ ልከፍትለት ተነሣሁ፤

በከርቤ ነጠብጣብ የራሱት እጆቼ፣

በከርቤም ፈሳሽ የተነከሩት ጣቶቼ፣

የመወርወሪያውን እጀታ ያዙ።

6ለውዴ ከፈትሁለት፤

ውዴ ግን አልነበረም፤ ሄዷል፤

በመሄዱም ልቤ ደነገጠ፤5፥6 ወይም በተናገረ ጊዜ ልቤ ወደ እርሱ ሄደ

ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም፤

ጠራሁት፤ ነገር ግን አልመለሰልኝም።

7የከተማዪቱም ጠባቂዎች፣

በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ አገኙኝ፤

እነዚህ የቅጥሩ ጠባቂዎች፣

ደበደቡኝ፤ አቈሰሉኝ፤

ልብሴንም ገፈፉኝ።

8እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፤

እማጠናችኋለሁ፤

ውዴን ካገኛችሁት፣

ምን ትሉት መሰላችሁ?

በፍቅሩ መታመሜን ንገሩት።

ባልንጀሮቿ

9አንቺ ከሴቶች ሁሉ የተዋብሽ ሆይ፤

ውድሽ ከሌሎች እንዴት ቢበልጥ ነው?

እስከዚህ የምትማጠኚንስ፣

ውድሽ ከሌሎች እንዴት ቢበልጥ ነው?

ሙሽራዪቱ

10ውዴ ፍልቅልቅና ደመ ግቡ ነው፤

ከዐሥር ሺሆችም የሚልቅ ነው።

11ራሱ የጠራ ወርቅ፣

ጠጕሩ ዞማ፣

እንደ ቍራም የጠቈረ ነው።

12ዐይኖቹ፣

በጅረት አጠገብ እንዳሉ ርግቦች፣

በወተት የታጠቡ፣

እንደ ዕንቍም ጕብ ጕብ ያሉ ናቸው።

13ጕንጮቹ የሽቱ መዐዛ የሚያመጡ፣

የቅመማ ቅመም መደቦችን ይመስላሉ፤

ከንፈሮቹም ከርቤ እንደሚያንጠባጥቡ፣

ውብ አበቦች ናቸው።

14ክንዶቹ በዕንፈርጥ ያጌጠ፣

የወርቅ ዘንግን ይመስላሉ፤

ሰውነቱም በሰንፔር ፈርጥ5፥14 ወይም ላፒስ ላዙሊ ያጌጠ፣

አምሮ የተሠራ የዝኆን ጥርስን ይመስላል።

15እግሮቹ በንጹሕ ወርቅ መቆሚያ ላይ የተተከሉ፣

የዕብነ በረድ ምሰሶዎችን ይመስላሉ፤

መልኩ እንደ ሊባኖስ ነው፤

እንደ ዝግባ ዛፎቹም ምርጥ ነው።

16አፉ ራሱ ጣፋጭ ነው፤

ሁለንተናውም ያማረ ነው።

እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፤

ውዴ ይህ ነው፤ ባልንጀራዬም እርሱ ነው።

Ketab El Hayat

نشيد الأنشاد 5:1-16

1(المُحِبُّ): قَدْ جِئْتُ إِلَى جَنَّتِي يَا أُخْتِي، يَا عَرُوسِي، وَقَطَفْتُ مُرِّي مَعَ أَطْيَابِي، وَأَكَلْتُ شَهْدِي مَعَ عَسَلِي، وَشَرِبْتُ خَمْرِي مَعَ لَبَنِي.

(بَنَاتُ أُورُشَلِيمَ): كُلُوا أَيُّهَا الْخُلّانُ. اشْرَبُوا حَتَّى الانْتِشَاءِ أَيُّهَا المُحِبُّونَ.

2(الْمَحْبُوبَةُ): قَدْ نِمْتُ وَلَكِنَّ قَلْبِي كَانَ مُسْتَيْقِظاً. آهِ، اسْمَعُوا! هَا صَوْتُ حَبِيبِي قَارِعاً قَائِلاً: افْتَحِي لِي يَا أُخْتِي، يَا حَبِيبَتِي، يَا حَمَامَتِي، يَا كَامِلَتِي! فَإِنَّ رَأْسِي قَدِ ابْتَلَّ مِنَ النَّدَى وَشَعْرِي مِنْ طَلِّ اللَّيْلِ.

3فَقُلْتُ: قَدْ خَلَعْتُ ثَوْبِي فَكَيْفَ أَرْتَدِيهِ ثَانِيَةً؟ غَسَلْتُ قَدَمَيَّ فَكَيْفَ أُوَسِّخُهُمَا؟ 4مَدَّ حَبِيبِي يَدَهُ مِنْ كُوَّةِ الْبَابِ، فَتَحَرَّكَتْ لَهُ مَشَاعِرِي، 5فَنَهَضْتُ لأَفْتَحَ لَهُ بِيَدَيْنِ تَقْطُرَانِ مُرّاً، وَأَصَابِعَ تَفِيضُ عِطْراً عَلَى مِزْلاجِ الْبَابِ. 6فَتَحْتُ لِحَبِيبِي، لَكِنَّ حَبِيبِي كَانَ قَدِ انْصَرَفَ وَعَبَرَ فَفَارَقَتْنِي نَفْسِي حِينَ ابْتَعَدَ. بَحَثْتُ عَنْهُ فَلَمْ أَجِدْهُ، دَعَوْتُهُ فَلَمْ يُجِبْ. 7وَجَدَنِي الْحُرَّاسُ الْمُتَجَوِّلُونَ فِي الْمَدِينَةِ، فَانْهَالُوا عَلَيَّ ضَرْباً فَجَرَحُونِي. نَزَعَ حُرَّاسُ الأَسْوَارِ رِدَائِي عَنِّي. 8أَسْتَحْلِفُكُنَّ يَا بَنَاتِ أُورُشَلِيمَ إِنْ وَجَدْتُنَّ حَبِيبِي أَنْ تُبَلِّغْنَهُ أَنِّي مَرِيضَةٌ حُبّاً.

9(بَنَاتُ أُورُشَلِيمَ): بِمَ يَفُوقُ حَبِيبُكِ الْمُحِبِّينَ أَيَّتُهَا الْجَمِيلَةُ بَيْنَ النِّسَاءِ؟ بِمَ يَفُوقُ حَبِيبُكِ الْمُحِبِّينَ حَتَّى تَسْتَحْلِفِينَا هَكَذَا؟

10(الْمَحْبُوبَةُ): حَبِيبِي مُتَأَلِّقٌ وَأَحْمَرُ، مُتَمَيِّزٌ بَيْنَ الآلَافِ. 11رَأْسُهُ ذَهَبٌ خَالِصٌ وَشَعْرُهُ مُتَمَوِّجٌ حَالِكُ السَّوَادِ كَلَوْنِ الْغُرَابِ. 12عَيْنَاهُ حَمَامَتَانِ عِنْدَ مَجَارِي الْمِيَاهِ، مَغْسُولَتَانِ مُسْتَقِرَّتَانِ فِي مَوْضِعِهِمَا. 13خَدَّاهُ كَخَمِيلَةِ طِيبٍ تَفُوحَانِ عِطْراً، وَشَفَتَاهُ كَالسَّوْسَنِ تَقْطُرَانِ مُرّاً شَذِيّاً. 14يَدَاهُ حَلَقَتَانِ مِنْ ذَهَبٍ مُدَوَّرَتَانِ وَمُرَصَّعَتَانِ بِالزَّبَرْجَدِ، وَجِسْمُهُ عَاجٌ مَصْقُولٌ مُغَشّىً بِالْيَاقُوتِ الأَزْرَقِ. 15سَاقَاهُ عَمُودَا رُخَامٍ قَائِمَتَانِ عَلَى قَاعِدَتَيْنِ مِنْ ذَهَبٍ نَقِيٍّ، طَلْعَتُهُ كَلُبْنَانَ، كَأَبْهَى أَشْجَارِ الأَرْزِ. 16فَمُهُ عَذْبٌ، وَكُلُّهُ مُشْتَهَيَاتٌ. هَذَا هُوَ حَبِيبِي وَهَذَا هُوَ خَلِيلِي يَا بَنَاتِ أُورُشَلِيمَ!