ማሕልየ መሓልይ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 3:1-11

1ሌሊቱን ሙሉ በዐልጋዬ ላይ ሆኜ፣

ውዴን ተመኘሁ፤

ተመኘሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

2ተነሥቼ ወደ ከተማዪቱ እወጣለሁ፤

በዋና ዋና መንገዶችና በአደባባዮች እዘዋወራለሁ፤

ውዴንም እፈልገዋለሁ፤

ስለዚህም ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

3በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ፣

የከተማዪቱ ጠባቂዎች አገኙኝ፤

እኔም፣ “ውዴን አይታችኋል?”

አልኋቸው።

4ከእነርሱ ጥቂት ዕልፍ እንዳልሁ፣

ውዴን አገኘሁት፤ ያዝሁት፤

ወደ እናቴ ቤት እስካመጣው፣

በማሕፀን ወደ ተሸከመችኝም ዕልፍኝ

እስካገባው ድረስ አልለቀውም።

5እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤

ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣

ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት፣

በሚዳቋና በሜዳ ዋሊያ አማጥናችኋለሁ።

6ከከርቤና ከዕጣን፣

ከነጋዴም ቅመማ ቅመም ሁሉ በተዘጋጀ ሽቱ፣

መዐዛዋ የሚያውድ፣

እንደ ጢስ ዐምድ ከምድረ በዳ የምትወጣው ይህች ማን ናት?

7እነሆ፤ የሰሎሞን ሠረገላ

በታዋቂዎቹ የእስራኤል መኳንንት፣

ስድሳ ጦረኞች ታጅባለች፤

8ሁሉም ሰይፍ የታጠቁ፣

ሁሉም በጦርነት የተፈተኑ ናቸው፤

የሌሊት አደጋን ለመከላከልም፣

እያንዳንዳቸው ሰይፋቸውን በወገባቸው ታጥቀዋል።

9ንጉሥ ሰሎሞን የራሱን ሠረገላ ሠራ፤

የሠራውም ከሊባኖስ በመጣ ዕንጨት ነው።

10ምሰሶዎቹን ከብር፣

መደገፊያውንም ከወርቅ ሠራ፤

መቀመጫውም በሐምራዊ ሐር የተሸፈነ ነው፤

ውስጡም በኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፣

አምሮ የተለበጠ ነው።3፥10 ወይም የተለበጠውም ውስጥ፣ ከኢየሩሳሌም ቈነጃጅት የሆነ የፍቅር ስጦታ

11እናንት የጽዮን ቈነጃጅት ውጡ፤

ንጉሥ ሰሎሞን አክሊሉን ደፍቶ እዩት፤

ዘውዱም ልቡ ሐሤት ባደረገባት፣

በዚያች በሰርጉ ዕለት፣

እናቱ የደፋችለት ነው።

Thai New Contemporary Bible

เพลงโซโลมอน 3:1-11

1ตลอดคืนบนเตียงของดิฉัน

ดิฉันมองหาพ่อยอดดวงใจ

เฝ้าชะแง้แลหาแต่ไม่พบ

2ดิฉันจะลุกขึ้นเดี๋ยวนี้ และไปทั่วเมือง

ไปตามถนนและลานเมือง

ดิฉันจะค้นหาพ่อยอดดวงใจของดิฉัน

แต่หาแล้วก็ไม่พบ

3ยามรักษาการณ์มาพบดิฉันเข้า

ขณะที่พวกเขากำลังตระเวนไปรอบเมือง

ดิฉันถามเขาว่า “เห็นพ่อยอดดวงใจของดิฉันไหม?”

4พอคล้อยหลังพวกเขาไปไม่เท่าไร

ดิฉันก็พบพ่อยอดดวงใจ

ดิฉันโอบกอดเขาไว้ไม่ยอมให้ไปไหน

จนพาเขามาถึงที่บ้านแม่ของดิฉัน

มาถึงห้องผู้ให้กำเนิดดิฉัน

5บรรดาสตรีชาวเยรูซาเล็มเอ๋ย

เรากำชับเจ้าด้วยพลังอย่างละมั่งและกวางในท้องทุ่งว่า

อย่าปลุกเร้าความรัก

แต่ปล่อยให้เป็นไปตามครรลองของมัน

6ใครหนอรีบรุดมาจากทะเลทราย?

ประหนึ่งลำหมอกควัน

อบอวลด้วยกลิ่นหอมของมดยอบและกำยาน

ที่ปรุงจากเครื่องหอมของพ่อค้า

7ดูสิ! นั่นคือราชยานของโซโลมอน

มีนักรบหกสิบคนคุ้มกันเป็นผู้เกรียงไกรที่สุดของอิสราเอล

8ทุกคนเป็นนักรบเจนศึก

ล้วนสะพายดาบ

เตรียมพร้อมรับภัยจู่โจมแห่งรัตติกาล

9กษัตริย์โซโลมอนทรงให้ประกอบราชยานนี้สำหรับพระองค์เอง

ด้วยไม้จากเลบานอน

10เสาราชยานทำด้วยเงิน

แท่นเป็นทอง พระที่นั่งบุผ้าสีม่วง

ภายในตกแต่งอย่างงดงาม

โดย3:10 หรือภายในตกแต่งด้วยของขวัญแห่งรัก / จากฝีมือบรรดาสตรีชาวเยรูซาเล็ม

11บรรดาสตรีแห่งศิโยน3:11 คือ บรรดาสตรีชาวเยรูซาเล็ม ออกมาเถิด

มาดูกษัตริย์โซโลมอนทรงมงกุฎ

ซึ่งราชมารดาทรงสวมให้

ในวันอภิเษกสมรส

วันแห่งความชื่นชมยินดีของพระองค์