መዝሙር 98 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 98:1-9

መዝሙር 98

የዓለም ሁሉ ዳኛ

መዝሙር።

1ለእግዚአብሔር አዲስ ዝማሬ አቅርቡ፤

እርሱ ድንቅ ነገሮችን አድርጓልና፤

ቀኝ እጁ፣ ቅዱስ ክንዱም

ማዳንን አድርገውለታል።

2እግዚአብሔር ማዳኑን አሳወቀ፤

ጽድቁንም በሕዝቦች ፊት ገለጠ።

3ለእስራኤል ቤት ምሕረቱን፣

ታማኝነቱንም ዐሰበ፤

የምድር ዳርቻዎችም ሁሉ፣

የአምላካችንን ማዳን አዩ።

4ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር እልል በሉ፤

ውዳሴን አፍልቁ፤ በደስታና በዝማሬ አመስግኑ፤

5ለእግዚአብሔር በገና ደርድሩለት፤

በበገናና በዝማሬ ድምፅ ዘምሩለት፤

6በእንቢልታና በመለከት ድምፅ፣

በንጉሡ በእግዚአብሔር ፊት እልል በሉ።

7ባሕርና በውስጧ ያለው ሁሉ፣

ዓለምና የሚኖሩባትም ሁሉ ያስገምግሙ።

8ወንዞች በእጃቸው ያጨብጭቡ፣

ተራሮችም በአንድነት ይዘምሩ፤

9እነዚህ በእግዚአብሔር ፊት ይዘምሩ፤

እርሱ በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣልና፤

በዓለም ላይ በጽድቅ፣

በሕዝቦችም ላይ በእውነት ይበይናል።

Ketab El Hayat

مزمور 98:1-9

الْمَزْمُورُ الثَّامِنُ وَالتِّسْعُونَ

1رَنِّمُوا لِلرَّبِّ تَرْنِيمَةً جَدِيدَةً، لأَنَّهُ قَدْ صَنَعَ عَجَائِبَ. وَبِيَمِينِهِ وَذِرَاعِهِ الْمُقَدَّسَةِ أَحْرَزَ خَلاصاً. 2أَعْلَنَ الرَّبُّ خَلاصَهُ؛ أَمَامَ أَنْظَارِ الأُمَمِ كَشَفَ بِرَّهُ. 3ذَكَرَ رَحْمَتَهُ وَأَمَانَتَهُ لِبَيْتِ إِسْرَائِيلَ. رَأَتْ كُلُّ أَقَاصِي الأَرْضِ خَلاصَ إِلَهِنَا.

4اهْتِفُوا لِلرَّبِّ يَا سَاكِنِي الأَرْضِ، اهْتِفُوا فَرَحاً وَرَنِّمُوا وَأَنْشِدُوا. 5أَنْشِدُوا لِلرَّبِّ بِعَزْفِ عُودٍ وَبِصَوْتِ نَشِيدٍ. 6اهْتِفُوا أَمَامَ الرَّبِّ الْمَلِكِ نَافِخِينَ بِأَبْوَاقٍ نُحَاسِيَّةٍ وَأَبْوَاقٍ قَرْنِيَّةٍ. 7لِيَهْتِفِ الْبَحْرُ بِأَمْوَاجِهِ وَبِكُلِّ مَا فِيهِ، وَالْمَسْكُونَةُ أَيْضاً وَمَنْ عَلَيْهَا. 8لِتُصَفِّقِ الأَنْهَارُ بِالأَيْدِي، وَتَتَرَنَّمِ الْجِبَالُ مَعاً. 9أَمَامَ الرَّبِّ لأَنَّهُ جَاءَ لِيَدِينَ الأَرْضَ بالْعَدْلِ وَالشُّعُوبَ بِالإِنْصَافِ.