መዝሙር 77 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 77:1-20

መዝሙር 77

የእስራኤል ጥንተ ነገር አሰላስሎ

ለመዘምራን አለቃ፤ ለኤዶታም፤ የአሳፍ መዝሙር።

1ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፤

ይሰማኝም ዘንድ ወደ አምላክ ጮኽሁ።

2በመከራዬ ቀን እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤

በሌሊትም ያለ ድካም እጆቼን ዘረጋሁ፤

ነፍሴም አልጽናና አለች።

3አምላክ ሆይ፤ አንተን ባሰብሁ ቍጥር ቃተትሁ፤

ባወጣሁ ባወረድሁም መጠን መንፈሴ ዛለች። ሴላ

4ዐይኖቼ እንዳይከደኑ ያዝሃቸው፤

መናገር እስኪሳነኝ ድረስ ታወክሁ።

5የድሮውን ዘመን አሰብሁ፤

የጥንቶቹን ዓመታት አውጠነጠንሁ።

6ዝማሬዬን በሌሊት አስታወስሁ፤

ከልቤም ጋር ተጫወትሁ፤ መንፈሴም ተነቃቅቶ እንዲህ ሲል ጠየቀ፦

7“ለመሆኑ፣ ጌታ ለዘላለም ይጥላልን?

ከእንግዲህስ ከቶ በጎነትን አያሳይምን?

8ምሕረቱስ ለዘላለም ጠፋን?

የገባውስ ቃል እስከ ወዲያኛው ተሻረን?

9እግዚአብሔር ቸርነቱን ዘነጋ?

ወይስ ከቍጣው የተነሣ ርኅራኄውን ነፈገ?” ሴላ

10እኔም፣ “የልዑል ቀኝ እጅ እንደ ተለወጠ ማሰቤ፣

ይህ ድካሜ ነው” አልሁ።

11የእግዚአብሔርን ሥራ አስታውሳለሁ፤

የጥንት ታምራትህን በርግጥ አስታውሳለሁ፤

12ሥራህን ሁሉ አሰላስላለሁ፤

ድንቅ ሥራህን ሁሉ አውጠነጥናለሁ።

13አምላክ ሆይ፤ መንገድህ ቅዱስ ነው፤

እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማን ነው?

14ታምራትን የምታደርግ አምላክ አንተ ነህ፤

በሕዝቦችም መካከል ኀይልህን ትገልጣለህ።

15የያዕቆብንና የዮሴፍን ልጆች፣

ሕዝብህን በክንድህ ተቤዠሃቸው። ሴላ

16አምላክ ሆይ፤ ውሆች አዩህ፤

ውሆች አንተን አይተው ተሸማቀቁ፤

ጥልቆችም ተነዋወጡ።

17ደመናት ውሃን አንጠባጠቡ፤

ሰማያት አንጐደጐዱ፤

ፍላጾችህም ዙሪያውን አብለጨለጩ።

18የነጐድጓድህ ድምፅ በዐውሎ ነፋስ ውስጥ ተሰማ፤

መብረቅህ ዓለምን አበራው፤

ምድርም ራደች፤ ተንቀጠቀጠች።

19መንገድህ በባሕር ውስጥ ነው፤

መሄጃህም በታላቅ ውሃ ውስጥ ነው፤

ዱካህ ግን አልታወቀም።

20በሙሴና በአሮን እጅ፣

ሕዝብህን እንደ በግ መንጋ መራኸው።

New International Version

Psalms 77:1-20

Psalm 77In Hebrew texts 77:1-20 is numbered 77:2-21.

For the director of music. For Jeduthun. Of Asaph. A psalm.

1I cried out to God for help;

I cried out to God to hear me.

2When I was in distress, I sought the Lord;

at night I stretched out untiring hands,

and I would not be comforted.

3I remembered you, God, and I groaned;

I meditated, and my spirit grew faint.77:3 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here and at the end of verses 9 and 15.

4You kept my eyes from closing;

I was too troubled to speak.

5I thought about the former days,

the years of long ago;

6I remembered my songs in the night.

My heart meditated and my spirit asked:

7“Will the Lord reject forever?

Will he never show his favor again?

8Has his unfailing love vanished forever?

Has his promise failed for all time?

9Has God forgotten to be merciful?

Has he in anger withheld his compassion?”

10Then I thought, “To this I will appeal:

the years when the Most High stretched out his right hand.

11I will remember the deeds of the Lord;

yes, I will remember your miracles of long ago.

12I will consider all your works

and meditate on all your mighty deeds.”

13Your ways, God, are holy.

What god is as great as our God?

14You are the God who performs miracles;

you display your power among the peoples.

15With your mighty arm you redeemed your people,

the descendants of Jacob and Joseph.

16The waters saw you, God,

the waters saw you and writhed;

the very depths were convulsed.

17The clouds poured down water,

the heavens resounded with thunder;

your arrows flashed back and forth.

18Your thunder was heard in the whirlwind,

your lightning lit up the world;

the earth trembled and quaked.

19Your path led through the sea,

your way through the mighty waters,

though your footprints were not seen.

20You led your people like a flock

by the hand of Moses and Aaron.