መዝሙር 75 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 75:1-10

መዝሙር 75

ለመለኮታዊው ዳኛ የቀረበ ዝማሬ

ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዜም፤ የአሳፍ መዝሙር ማሕሌት።

1አምላክ ሆይ፤ ምስጋና እናቀርብልሃለን፤

ስምህ ቅርብ ነውና ምስጋና እናቀርብልሃለን፤

ሰዎችም ስለ ድንቅ ሥራህ ይናገራሉ።

2አንተም እንዲህ አልህ፤ “ለይቼ በወሰንኋት ሰዓት፣

በቅን የምፈርድ እኔ ነኝ።

3ምድርና ሕዝቦቿ ሁሉ በሚናወጡበት ጊዜ፣

ምሰሶዎቿን አጽንቼ የምይዝ እኔ ነኝ። ሴላ

4እብሪተኛውን፣ ‘አትደንፋ’፤

ክፉውንም ‘ቀንድህን ከፍ አታድርግ እለዋለሁ፤

5ቀንድህን ወደ ሰማይ አታንሣ፤

ዐንገትህንም መዝዘህ አትናገር።’ ”

6ክብር ከምሥራቅ ወይም ከምዕራብ፣

ወይም ከምድረ በዳ አይመጣምና፤

7ነገር ግን የሚፈርድ እግዚአብሔር ነው፤

እርሱ አንዱን ዝቅ፣ ሌላውን ከፍ ያደርጋል።

8በእግዚአብሔር እጅ ጽዋ አለ፤

በሚገባ የተቀመመና ዐረፋ የሚወጣው የወይን ጠጅ ሞልቶበታል፤

ይህን ከውስጡ ወደ ውጭ ገለበጠው፤

የምድር ዐመፀኞችም አተላውን ሳይቀር ይጨልጡታል።

9እኔ ግን ይህን ለዘላለም ዐውጃለሁ፤

ለያዕቆብም አምላክ ዝማሬ አቀርባለሁ።

10የክፉዎችን ሁሉ ቀንድ እሰብራለሁ፤

የጻድቃን ቀንድ ግን ከፍ ከፍ ይላል።

King James Version

Psalms 75:1-10

To the chief Musician, Al-taschith, A Psalm or Song of Asaph.

1Unto thee, O God, do we give thanks, unto thee do we give thanks: for that thy name is near thy wondrous works declare.75.1 Al-taschith: or, Destroy not75.1 of: or, for

2When I shall receive the congregation I will judge uprightly.75.2 receive…: or, take a set time

3The earth and all the inhabitants thereof are dissolved: I bear up the pillars of it. Selah.

4I said unto the fools, Deal not foolishly: and to the wicked, Lift not up the horn:

5Lift not up your horn on high: speak not with a stiff neck.

6For promotion cometh neither from the east, nor from the west, nor from the south.75.6 south: Heb. desert

7But God is the judge: he putteth down one, and setteth up another.

8For in the hand of the LORD there is a cup, and the wine is red; it is full of mixture; and he poureth out of the same: but the dregs thereof, all the wicked of the earth shall wring them out, and drink them.

9But I will declare for ever; I will sing praises to the God of Jacob.

10All the horns of the wicked also will I cut off; but the horns of the righteous shall be exalted.