መዝሙር 72 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 72:1-20

መዝሙር 72

በተስፋ የሚጠባበቀው ንጉሥ

ስለ ሰሎሞን።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍትሕን ለንጉሥ፣

ጽድቅህንም ለንጉሥ ልጅ ዐድል፤

2እርሱም ሕዝብህን በጽድቅ ይዳኛል፤72፥2 ወይም እርሱ ሕዝቡን በጽድቅ ይዳኝ

ለተቸገሩትም በትክክል ይፈርዳል።

3ተራሮች ብልጽግናን፣

ኰረብቶችም የጽድቅን ፍሬ ለሕዝቡ ያመጣሉ።

4ለተቸገረው ሕዝብ ይሟገታል፤

የድኾችን ልጆች ያድናል፤

ጨቋኙንም ያደቅቀዋል።

5ፀሓይ እስካለች ድረስ፣

ጨረቃም በምትኖርበት ዘመን ሁሉ፣ ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።72፥5 ወይም የተፈራ ይሆናል

6እንደ ዝናብ በታጨደ መስክ ላይ ይወርዳል፤

እንደ ካፊያም ምድርን ያረሰርሳል።

7በዘመኑ ጽድቅ ይሰፍናል፤

ጨረቃ ከስፍራዋ እስከምትታጣ ድረስም ሰላም ይበዛል።

8ከባሕር እስከ ባሕር ድረስ፣

ከታላቁም ወንዝ72፥8 የኤፍራጥስ ወንዝ ነው። እስከ ምድር ዳርቻ ይገዛል።

9የበረሓ ዘላኖች በፊቱ ይሰግዳሉ፤

ጠላቶቹም ዐፈር ይልሳሉ።

10የተርሴስና የደሴቶች ነገሥታት፣

ግብር ያመጡለታል፤

የዐረብና የሳባ ነገሥታት፣

እጅ መንሻ ያቀርባሉ።

11ነገሥታት ሁሉ ይሰግዱለታል፤

ሕዝቦችም ሁሉ ይገዙለታል።

12ችግረኛው በጮኸ ጊዜ፣

ምስኪኑንና ረዳት የሌለውን ይታደገዋል።

13ለድኾችና ለችግረኞች ይራራል፤

ምስኪኖችንም ከሞት ያድናል።

14ሕይወታቸውን ከጭቈናና ከግፍ ያድናል፤

ደማቸውም በእርሱ ፊት ክቡር ነው።

15ዕድሜው ይርዘም!

ከዐረብ ወርቅ ይምጣለት፤

ዘወትር ይጸልዩለት፤

ቀኑንም ሙሉ ይባርኩት።

16በምድሪቱ ላይ እህል ይትረፍረፍ፤

በተራሮችም ዐናት ላይ ይወዛወዝ።

ፍሬው እንደ ሊባኖስ ይንዠርገግ፤

በከተማ ያለውም እንደ ሜዳ ሣር እጅብ ብሎ ይውጣ።

17ስሙ ለዘላለም ጸንቶ ይኑር፤

ዝናው ፀሓይ የምትኖረውን ዘመን ያህል ይዝለቅ።

ሕዝቦች ሁሉ በእርሱ ይባረኩ፤

ሕዝቡ ሁሉ ቡሩክ ነህ ይበለው።

18ብቻውን ድንቅ ነገር የሚያደርግ፣

የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይባረክ።

19ክቡር ስሙ ለዘላለም ይባረክ፤

ምድርም ሁሉ በክብሩ ይሞላ።

አሜን፤ አሜን።

20የእሴይ ልጅ የዳዊት ጸሎት እዚህ ላይ ተፈጸመ።

Ketab El Hayat

مزمور 72:1-20

الْمَزْمُورُ الثَّانِي وَالسَّبْعُونَ

لِسُلَيْمَانَ

1اللهُمَّ أَعْطِ أَحْكَامَكَ الْعَادِلَةَ لِلْمَلِكِ ولابْنِهِ بِرَّكَ، 2فَيَقْضِيَ لِشَعْبِكَ بِالْعَدْلِ وَمَسَاكِينِكَ بِالإِنْصَافِ. 3لِتَحْمِلِ الْجِبَالُ لِلشَّعْبِ سَلاماً، وَالتِّلالُ بِرّاً. 4لِيَحْكُمِ الْمَلِكُ بِالْحَقِّ لِلْمَسَاكِينِ، وَيُنْقِذْ بَنِي الْبَائِسِينَ، وَيُحَطِّمِ الظَّالِمَ. 5لِيَرْهَبُوكَ مَادَامَتِ الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ، مِنْ جِيلٍ إِلَى جِيلٍ. 6لِيَكُنِ الْمَلِكُ كَالْمَطَرِ الْمُنْهَمِرِ عَلَى الْمَرَاعِي الْمَجْزُوزَةِ، كَالْغُيُوثِ الَّتِي تَسْقِي الأَرْضَ. 7لِيَزْدَهِرْ فِي أَيَّامِهِ الصِّدِّيقُ، وَيَتَوَافَرِ السَّلامُ مَادَامَ الْقَمَرُ يُضِيءُ. 8وَلْتَمْتَدَّ مَمْلَكَتُهُ مِنَ الْبَحْرِ إِلَى الْبَحْرِ، وَمِنَ النَّهْرِ إِلَى أَقَاصِي الأَرْضِ.

9أَمَامَهُ يَرْكَعُ أَهْلُ الْبَادِيَةِ، وَأَعْدَاؤُهُ يَلْحَسُونَ التُّرَابَ. 10مُلُوكُ تَرْشِيشَ وَالْجُزُرِ يَحْمِلُونَ إِلَيْهِ الْهَدَايَا. مُلُوكُ شَبَا وَسَبَأَ يُقَدِّمُونَ عَطَايَا. 11يَنْحَنِي أَمَامَهُ جَمِيعُ الْمُلُوكِ. وَتَتَعَبَّدُ لَهُ كُلُّ الأُمَمِ. 12لأَنَّهُ يُنْقِذُ الْمِسْكِينَ الْمُسْتَغِيثَ الْبَائِسَ الَّذِي لَا مُعِينَ لَهُ. 13يَعْطِفُ عَلَى الْفَقِيرِ وَالْمُحْتَاجِ وَيُخَلِّصُ نُفُوسَ الْمَسَاكِينِ. 14إِذْ يَفْتَدِي نُفُوسَهُمْ مِنَ الظُّلْمِ وَالْعُنْفِ، وَيَحْفَظُ حَيَاتَهُمْ لأَنَّهَا ثَمِينَةٌ فِي عَيْنَيْهِ. 15لِيَحْيَ الْمَلِكُ! لِيُعْطَ لَهُ ذَهَبُ شَبَا. وَلْيُصَلُّوا مِنْ أَجْلِهِ دَائِماً وَيَطْلُبُوا لَهُ بَرَكَةَ اللهِ كُلَّ النَّهَارِ.

16لِتَتَكَاثَرِ الْغِلالُ فِي الأَرْضِ وَعَلَى رُؤُوسِ الْجِبَالِ، وَتَتَمَاوَجْ مِثْلَ أَرْزِ لُبْنَانَ، وَيُزْهِرْ أَهْلُ الْمَدِينَةِ كَعُشْبِ الأَرْضِ. 17يَخْلُدُ اسْمُهُ إِلَى الدَّهْرِ، وَيَدُومُ اسْمُهُ كَدَيْمُومَةِ الشَّمْسِ، وَيَتَبَارَكُ النَّاسُ بِهِ، وَتُطَوِّبُهُ كُلُّ الأُمَمِ. 18تَبَارَكَ الرَّبُّ إِلَهُ إِسْرَائِيلَ، فَهُوَ وَحْدَهُ صَانِعُ الْعَجَائِبِ. 19تَبَارَكَ اسْمُهُ الْمَجِيدُ إِلَى الأَبَدِ، وَلْتَمْتَلِئِ الأَرْضُ كُلُّهَا مِنْ مَجْدِهِ. آمِين ثُمَّ آمِين.

20هُنَا تَنْتَهِي صَلَوَاتُ دَاوُدَ بْنِ يَسَّى.