መዝሙር 70 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 70:1-5

መዝሙር 70

የጭንቀት ጩኸት

70፥1-5 ተጓ ምብ – መዝ 40፥13-17

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር፤ ለመታሰቢያ።

1አምላክ ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ዘንበል በል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

2ሕይወቴን ለማጥፋት የሚሹ፣

ይፈሩ፤ ሁከትም ይምጣባቸው፤ የእኔን መጐዳት የሚመኙ፣

በውርደት ወደ ኋላቸው ይመለሱ።

3በእኔ ላይ፣ “ዕሠይ! ዕሠይ!” የሚሉ፣

ተሸማቅቀው ወደ ኋላ ይመለሱ።

4ነገር ግን የሚሹህ ሁሉ፣

በአንተ ሐሤት ያድርጉ፤ ደስም ይበላቸው፤

“ማዳንህን የሚወድዱ ሁሉ ሁልጊዜ፣

እግዚአብሔር ከፍ ይበል!” ይበሉ።

5እኔ ግን ምስኪንና ችግረኛ ነኝ፤

አምላክ ሆይ፤ ፈጥነህ ድረስልኝ፤

ረዳቴም፣ ታዳጊዬም አንተ ነህና፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ አትዘግይ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 70:1-5

第 70 篇

求助的祷告

大卫作的祷告诗,交给乐长。

1上帝啊,求你快快拯救我;

耶和华啊,求你速速帮助我。

2愿谋取我性命的人蒙羞受辱,

愿喜欢我遭害的人狼狈逃窜。

3愿那些哈哈嘲笑我的人羞愧而退。

4愿所有寻求你的人因你而欢喜快乐,

愿渴望蒙你拯救的人时常说:

“上帝当受尊崇!”

5我贫穷困苦,

上帝啊,求你快来救我。

你是我的帮助,是我的拯救。

耶和华啊,求你不要迟延。