መዝሙር 7 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 7:1-17

መዝሙር 7

በስደት ጊዜ የጻድቁ ሰው ጸሎት

ዳዊት በብንያማዊው በኩዝ ምክንያት ለእግዚአብሔር የዘመረው መዝሙር።

1እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ አንተ መሸሸጊያዬ ነህ፤

ከሚያሳድዱኝ ሁሉ አድነኝ፤ ታደገኝም፤

2አለዚያ እንደ አንበሳ ይዘነጣጥሉኛል፤

የሚያድነኝ በሌለበትም ይቦጫጭቁኛል።

3እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ይህን አድርጌ ከሆነ፣

በደልም በእጄ ከተገኘ፣

4በጎ ለዋለልኝ ክፉ መልሼ ብሆን፣

ጠላቴንም በከንቱ ዘርፌ ከሆነ፣

5ጠላቴ አሳድዶ ይያዘኝ፤

ሕይወቴን ከምድር ይቀላቅል፤

ክብሬንም ከዐፈር ይደባልቅ። ሴላ

6እግዚአብሔር ሆይ፤ በመዓትህ ተነሥ፤

በቍጣ በተነሡብኝ ላይ ተነሥ፤

አምላኬ ሆይ፤ ንቃ፤ ትእዛዝም አስተላልፍ!

7የሕዝቦች ጉባኤ ይክበብህ፤

አንተም ከላይ ሆነህ ግዛቸው፤

8እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ይፈርዳል።

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ጽድቄ ፍረድልኝ፤

ልዑል ሆይ፤ እንደ ቅን አካሄዴ መልስልኝ።

9ልብንና ኵላሊትን የምትመረምር፣

ጻድቅ አምላክ ሆይ፤

የክፉዎችን ዐመፅ አጥፋ፤

ጻድቁን ግን አጽና።

10ጋሻዬ7፥10 ወይም የእኔ ልዑል ልዑል አምላክ ነው፤

እርሱ ልበ ቅኖችን ያድናቸዋል።

11እግዚአብሔር ጻድቅ ዳኛ ነው፤

ቍጣውንም በየዕለቱ የሚገልጥ አምላክ ነው።

12ሰው በንስሓ የማይመለስ ከሆነ ግን፣

ሰይፉን7፥12 ወይም ሰው ንስሓ ካልገባ፣ እግዚአብሔር ሰይፉን ይስላል፤

ቀስቱን ይገትራል።

13የሚገድሉ ጦር ዕቃዎቹን አሰናድቷል፤

የሚንበለበሉትን ፍላጻዎቹንም አዘጋጅቷል።

14ክፋትን እያማጠ ያለ ሰው፣

ቅጥፈትን አርግዞ፣ ሐሰትን ይወልዳል።

15ጕድጓድ ምሶ ዐፈሩን የሚያወጣ፣

በአዘጋጀው ጕድጓድ ራሱ ይገባበታል።

16ተንኰሉ ወደ ራሱ ይመለሳል፤

ዐመፃውም በገዛ ዐናቱ ላይ ይወርዳል።

17ስለ ጽድቁ ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀርባለሁ፤

የልዑል እግዚአብሔርን ስም በመዝሙር አወድሳለሁ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 7:1-17

第 7 篇

求上帝伸張正義

大衛向耶和華唱的詩,與便雅憫人古實有關。

1我的上帝耶和華啊,我投靠你,

求你拯救我脫離追趕我的人。

2別讓他們像獅子般撕裂我,

無人搭救。

3我的上帝耶和華啊,

倘若我犯了罪,

手上沾了不義;

4倘若我恩將仇報,

無故搶奪仇敵,

5就讓仇敵追上我,

踐踏我,使我聲名掃地。(細拉)

6耶和華啊,

求你發怒攻擊我暴怒的仇敵。

我的上帝啊,

求你來伸張正義。

7願萬民環繞你,

願你從高天治理他們,

8願你審判萬民!

至高的耶和華啊,

我是公義正直的,

求你為我主持公道。

9鑒察人心肺腑的公義上帝啊,

求你剷除邪惡,扶持義人。

10上帝是我的盾牌,

祂拯救心地正直的人。

11上帝是公義的審判官,

天天向惡人發怒。

12他們若不悔改,祂必磨刀霍霍,

彎弓搭箭,誅滅他們。

13祂準備好了奪命的兵器,

火箭已在弦上。

14惡人心懷惡念,

居心叵測,滋生虛謊。

15他們挖了陷阱,卻自陷其中。

16他們的惡行臨到自己頭上,

他們的暴力落到自己腦殼上。

17我要稱謝耶和華的公義,

我要歌頌至高者耶和華的名。