መዝሙር 66 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 66:1-20

መዝሙር 66

የኅብረት ምስጋና

ለመዘምራን አለቃ፤ ማሕሌት፤ መዝሙር።

1ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር እልል ይበል!

2ለስሙ ክብር ዘምሩ፤

ውዳሴውንም አድምቁ

3እግዚአብሔርን እንዲህ በሉት፤ “ሥራህ እንዴት ግሩም ነው!

ጠላቶችህ ከኀይልህ ታላቅነት የተነሣ፣

በፊትህ ይርዳሉ።

4ምድር ሁሉ ይሰግድልሃል፤

በዝማሬ ያመሰግኑሃል፤

ለስምህም ይዘምራሉ።” ሴላ

5ኑና፣ እግዚአብሔር ያደረገውን እዩ፤

በሰዎች መካከል ሥራው አስፈሪ ነው!

6ባሕሩን የብስ አደረገው፤

ወንዙን በእግር ተሻገሩ፤

ኑ፣ በእርሱ ደስ ይበለን።

7በኀይሉ ለዘላለም ይገዛል፤

ዐይኖቹ ሕዝቦችን ይመለከታሉ፤

እንግዲህ ዐመፀኞች ቀና ቀና አይበሉ። ሴላ

8ሕዝቦች ሆይ፤ አምላካችንን ባርኩ፤

የምስጋናውንም ድምፅ አሰሙ።

9እኛን በሕይወት የሚያኖረን፣

እግራችንንም ከመንሸራተት የሚጠብቅ እርሱ ነው።

10አምላክ ሆይ፤ አንተ ፈተንኸን፤

እንደ ብርም አነጠርኸን።

11ወደ ወጥመድ አገባኸን፤

በጀርባችንም ሸክም ጫንህብን።

12ሰዎች በራሳችን ላይ እንዲፈነጩ አደረግህ፤

በእሳትና በውሃ መካከል ዐለፍን፤

የኋላ ኋላ ግን ወደ በረከት አመጣኸን።

13የሚቃጠል መሥዋዕት ይዤ ወደ መቅደስህ እገባለሁ፤

ስእለቴንም ለአንተ እፈጽማለሁ፤

14በመከራ ጊዜ ከአፌ የወጣ፣

በከንፈሬም የተናገርሁት ስእለት ነው።

15ፍሪዳዎችን የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጌ፣

አውራ በጎችንም የሚጤስ ቍርባን አድርጌ አቀርብልሃለሁ፤

ኰርማዎችንና ፍየሎችንም እሠዋልሃለሁ። ሴላ

16እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሁሉ፤ ኑና ስሙ፤

ለነፍሴ ያደረገላትን ልንገራችሁ።

17በአፌ ወደ እርሱ ጮኽሁ፤

በአንደበቴም አመሰገንሁት።

18ኀጢአትን በልቤ አስተናግጄ ቢሆን ኖሮ፣

ጌታ ባልሰማኝ ነበር።

19አሁን ግን እግዚአብሔር በርግጥ ሰምቶኛል፤

ጸሎቴንም አድምጧል።

20ጸሎቴን ያልናቀ፣

ምሕረቱንም ከእኔ ያላራቀ፣

እግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው።

New International Version – UK

Psalms 66:1-20

Psalm 66

For the director of music. A song. A psalm.

1Shout for joy to God, all the earth!

2Sing the glory of his name;

make his praise glorious.

3Say to God, ‘How awesome are your deeds!

So great is your power

that your enemies cringe before you.

4All the earth bows down to you;

they sing praise to you,

they sing the praises of your name.’66:4 The Hebrew has Selah (a word of uncertain meaning) here and at the end of verses 7 and 15.

5Come and see what God has done,

his awesome deeds for mankind!

6He turned the sea into dry land,

they passed through the waters on foot –

come, let us rejoice in him.

7He rules for ever by his power,

his eyes watch the nations –

let not the rebellious rise up against him.

8Praise our God, all peoples,

let the sound of his praise be heard;

9he has preserved our lives

and kept our feet from slipping.

10For you, God, tested us;

you refined us like silver.

11You brought us into prison

and laid burdens on our backs.

12You let people ride over our heads;

we went through fire and water,

but you brought us to a place of abundance.

13I will come to your temple with burnt offerings

and fulfil my vows to you –

14vows my lips promised and my mouth spoke

when I was in trouble.

15I will sacrifice fat animals to you

and an offering of rams;

I will offer bulls and goats.

16Come and hear, all you who fear God;

let me tell you what he has done for me.

17I cried out to him with my mouth;

his praise was on my tongue.

18If I had cherished sin in my heart,

the Lord would not have listened;

19but God has surely listened

and has heard my prayer.

20Praise be to God,

who has not rejected my prayer

or withheld his love from me!