መዝሙር 62 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 62:1-12

መዝሙር 62

ተስፋ በእግዚአብሔር ላይ ብቻ

ለመዘምራን አለቃ፤ ለኤዶታም፤ የዳዊት መዝሙር።

1ነፍሴ ዕረፍት የምታገኘው በእግዚአብሔር ብቻ ነው፤

ድነቴም የሚመጣልኝ ከእርሱ ዘንድ ነው።

2ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤

መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ ከቶም አልናወጥም።

3ሰውን የምታጠቁት እስከ መቼ ነው?

ይህን የዘመመ ግድግዳ፣ የተንጋደደ ዐጥር፣

ሁላችሁ ገፍታችሁ ልትጥሉት ትሻላችሁ?

4ከታላቅ ክብሩ ሊያዋርዱት፣

ይህን አንድ ነገር ወጠኑ፤

ሐሰት ባለበት ነገር ደስ ይሰኛሉ፤

በአፋቸው ይመርቃሉ፤

በልባቸው ግን ይራገማሉ። ሴላ

5ነፍሴ ሆይ፤ ዐርፈሽ እግዚአብሔርን ብቻ ጠብቂ፤

ተስፋዬ ከእርሱ ዘንድ ነውና።

6ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤

መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ እኔም አልናወጥም።

7መዳኔና ክብሬ በእግዚአብሔር ነው፤62፥7 ወይም ልዑል እግዚአብሔር ድነቴና ክብሬ ነው ተብሎ መተርጐም ይችላል።

ብርቱ ዐለቴና መሸሸጊያዬ በእግዚአብሔር ነው።

8ሰዎች ሆይ፤ ሁልጊዜ በእርሱ ታመኑ፤

ልባችሁን በፊቱ አፍስሱ፤

እግዚአብሔር መጠጊያችን ነውና። ሴላ

9ከተናቀ ወገን መወለድ ከንቱ፣

ከከበረውም መወለድ ሐሰት ነው።

በሚዛን ላይ ከፍ ብለው ቢታዩም፣

ሁሉም በአንድነት ከነፋስ የቀለሉ ናቸው።

10በዝርፊያ አትታመኑ፤

በቅሚያም ተስፋ አታድርጉ፤

በዚህ ብትበለጽጉም፣

ልባችሁ ይህን አለኝታ አያድርግ።

11እግዚአብሔር አንድ ነገር ተናገረ፤

እኔም ይህን ሁለት ጊዜ ሰማሁ፤

ኀይል የእግዚአብሔር ነው።

12ጌታ ሆይ፤ ምሕረትም የአንተ ነው፤

አንተ ለእያንዳንዱ፣

እንደ ሥራው ትከፍለዋለህ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 62:1-12

62

1私は黙って、神からの救いを待ちます。

救うことができるのは神だけですから。

2神こそ私の岩、私を救うお方、

そして私のとりでです。

ですから私は、困難にぶつかるときでも、

おじけづくことはありません。

3-4ところが、いったいどうしたことでしょう。

私の王座が揺らぐと、

人々はいっせいに非難をあびせかけてくるのです。

王位から追い落とそうと、策略を練り、

必死になって根も葉もないうわさを流します。

面と向かっては、いかにもにこやかにふるまうのに、

心の中ではのろっているのです。

5しかし、私はじっと黙って、神の救いを待ちます。

救うことができるのは神だけだからです。

6確かに、神だけが私の岩、私を救うお方、

そして私のとりでなのです。

ですから、困難に出会っても、

顔をこわばらせなくてよいのです。

7私が守られるのも、名声を獲得するのも、

神のお心ひとつです。

神は私の隠れ家、敵の手の届かない岩です。

8同胞よ。いつでも神への信頼を失わず、

心にある願いを洗いざらい申し上げなさい。

神はきっと助けてくださいます。

9身分の高い者も低い者も、

神の目から見ればみな無に等しく、

天秤で計れば、空気より軽いことがわかります。

10-11搾取と強奪によって財産を増やしてはいけません。

金持ちだからといって、尊大になってはいけません。

12愛と恵みに満ちた主は、

一人一人のしわざに報われるのです。