መዝሙር 60 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 60:1-12

መዝሙር 60

ከሽንፈት በኋላ የቀረበ ብሔራዊ ጸሎት

60፥5-12 ተጓ ምብ – መዝ 108፥6-13

ለመዘምራን አለቃ፤ “የኪዳን ጽጌረዳ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤60 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። በሰሜናዊ ምዕራብ መስጴጦምያና60 ርእሱ የአራማውያን ወይም የሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ነው። በማእከላዊ ሶርያ የሚኖሩትን አራማውያን60 ርእሱ በመካከለኛው ሶርያ የሚገኙት አራማውያንን የሚያመለክት ነው። በወጋቸው ጊዜ፣ ኢዮአብም ተመልሶ በጨው ሸለቆ ዐሥራ ሁለት ሺሕ ኤዶማውያንን በፈጀ ጊዜ፣ ለትምህርት፤ የዳዊት ቅኔ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ጣልኸን፤ አንኰታኰትኸን፤

ተቈጣኸንም፤ አሁን ግን መልሰህ አብጀን።

2ምድሪቱን አናወጥሃት፤ ፍርክስክስ አደረግሃት፤

ትንገዳገዳለችና ስብራቷን ጠግን።

3ለሕዝብህ አበሳውን አሳየኸው፤

ናላ የሚያዞር የወይን ጠጅ እንድንጠጣም ሰጠኸን።

4ነገር ግን ከቀስት እንዲያመልጡ፣

ለሚፈሩህ ምልክት አቆምህላቸው። ሴላ

5ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣

በቀኝ እጅህ ርዳን፤ መልስም ስጠን።

6እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

“ደስ እያለኝ የሴኬምን ምድር እሸነሽናለሁ፤

የሱኮትን ሸለቆ አከፋፍላለሁ።

7ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤

ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤

ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው።

8ሞዓብ የመታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤

በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤

በፍልስጥኤም ላይ በድል እልል እላለሁ።”

9ወደ ተመሸገው ከተማ ማን ያመጣኛል?

ማንስ ወደ ኤዶምያስ ይመራኛል?

10አምላክ ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?

እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰራዊታችን ጋር እኮ አልወጣ አልህ!

11በጠላት ላይ ድልን አቀዳጀን፤

የሰው ርዳታ ከንቱ ነውና።

12በእግዚአብሔር ክንደ ብርቱ እንሆናለን፤

ጠላቶቻችንን የሚረጋግጥልን እርሱ ነውና።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 60:1-12

60

ダビデがシリヤ(アラム)と戦い、戦況がまだはっきりしていなかったとき、司令官ヨアブが塩の谷でエドム人一万二千人を打ち殺した。その時のダビデの作。

1ああ神よ。

あなたは私たちを拒み、その守りをもくずされました。

御怒りにふれて、私たちは見捨てられたのです。

主よ、もう一度、情けをかけてください。

2あなたはこの国を恐怖で震撼させ、引き裂かれました。

主よ、深みまで揺るがされたこの地を今、

回復してください。

3さんざんに打ちのめされて、

私たちの足はよろめいています。

4-5しかし、あなたはこんな私たちを

奮起させるための旗を下さいました。

真理を愛する人々が、この旗のもとに集うためです。

そうしてこそ、あなたは愛する国民に

解放をもたらしてくださるのです。

どうか、力に満ちた右の手をふるって、

私たちを救い出してください。

6-7神は、ご自分の名誉にかけて

救援を約束してくださいました。

私は大いに喜びました。

神はこう宣言なさいます。

「シェケム、スコテ、ギルアデ、マナセは、

依然としてわたしのものだ。

ユダからは継続して王が出、

エフライムからは勇士が誕生する。

8モアブはわたしの召使となり、

エドムは奴隷となる。

わたしはまた、ペリシテを攻め取って、

勝利の声を上げよう。」

9-10あの強固なエドムの町に、

この私を入城させてくださるのはどなたでしょう。

それは神です。

私たちを捨てて敵の手に渡された、その神です。

11主よ、どうか敵の攻撃から守ってください。

人の助けなど、あてになりません。

12神の助けがあれば、

私たちは強力な働きを進めることができます。

神が敵を踏みつけてくださるからです。