መዝሙር 57 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 57:1-11

መዝሙር 57

በጨካኝ ጠላቶች ዘንድ

57፥7-11 ተጓ ምብ – መዝ 108፥1-5

ለመዘምራን አለቃ፤ “አታጥፋ” በሚለው ቅኝት የሚዘመር፤ ከሳኦል ፊት ሸሽቶ በዋሻ በነበረበት ጊዜ፤ የዳዊት ቅኔ57 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ማረኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ማረኝ፤

ነፍሴ አንተን መጠጊያ አድርጋለችና፤

በክንፎችህ ሥር እጠለላለሁ።

2ለእኔ ያሰበውን ወደሚፈጽምልኝ አምላክ፣

ወደ ልዑል እግዚአብሔር እጮኻለሁ።

3ከሰማይ ልኮ ያድነኛል፤

የረገጡኝን ያዋርዳቸዋል፤ ሴላ

እግዚአብሔር ምሕረቱንና ታማኝነቱን ይልካል።

4ነፍሴ በአንበሶች ተከብባለች፤

በሚዘነጣጥሉ አራዊት መካከል ወድቄአለሁ፤

እነዚህም፣ ጥርሳቸው ጦርና ፍላጻ፣

ምላሳቸውም የተሳለ ሰይፍ የሆኑ ሰዎች ናቸው።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።

6ለእግሬ ወጥመድን ዘረጉ፤

ነፍሴንም አጐበጧት፤

በመተላለፊያዬ ላይ ጕድጓድ ቈፈሩ፤

ነገር ግን ራሳቸው ገቡበት። ሴላ

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤

ልቤ ጽኑ ነው፤

እቀኛለሁ፤ አዜማለሁ።

8ነፍሴ ሆይ፤ ንቂ!

በገናና መሰንቆም ተነሡ

እኔም በማለዳ እነሣለሁ።

9ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤

በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ፤

10ምሕረትህ እስከ ሰማያት ከፍ ብላለችና፤

ታማኝነትህም እስከ ደመናት ትደርሳለች።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤

ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትስፈን።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 57:1-11

57

1ああ神よ、あなただけを頼りにしているこの私を、

あわれんでください。

嵐が過ぎ去るまで、御翼の陰に潜ませてください。

2私は、天におられる神、

奇跡を行ってくださる神に叫びます。

3すると、愛と真実の神は、

天から手を差し伸べて救ってくださいます。

私を亡き者にしようと、必死になっている

うそつきどもから、救ってくださるでしょう。

4私は、獰猛なライオンに囲まれているかのようです。

彼らは、まるで槍や矢のように鋭い歯をして、

気炎を上げています。

その舌は、まさしく剣です。

5主が、天より高くあがめられますように。

ご栄光を地上高く現してください。

6敵が罠をしかけたので、

私は言いようのない恐怖にとらわれています。

彼らはまた、私の通る道に落とし穴を掘りました。

しかし、そこに落ちたのは彼らのほうだったのです。

7ああ神よ。私の心は平安で、確信に満ちています。

あなたをたたえる歌が、自然に口をついて出ます。

8私のたましいよ、目を覚ませ。

十弦の琴と竪琴よ、身を起こせ。

さあ、歌って夜明けを待とう。

9私は国中を巡り、

人々の前で神に感謝をささげます。

諸国を行き巡り、あなたをたたえる歌を歌います。

10あなたの恵みと愛は、天そのもののように広大無辺です。

あなたの真実は、空よりも高くそびえています。

11ああ神よ。

あなたの名が天よりも高くあがめられますように。

ご栄光が全世界を照らしますように。