መዝሙር 56 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 56:1-13

መዝሙር 56

በእግዚአብሔር መደገፍ

ለመዘምራን አለቃ፤ “ርግቢቱ ሩቅ ባለው ወርካ ላይ” በተባለው ቅኝት፤ ፍልስጥኤማውያን በጌት በያዙት ጊዜ፤ የዳዊት ቅኔ56 ርእሱ የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ የሰዎች መረገጫ ሆኛለሁና ማረኝ፤

ቀኑንም ሙሉ በውጊያ አስጨንቀውኛል።

2ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ በላዬ ቆሙ፤

በትዕቢት የሚዋጉኝ ብዙዎች ናቸውና።

3ፍርሀት በሚይዘኝ ጊዜ፣

እምነቴን በአንተ ላይ አደርጋለሁ።

4ቃሉን በማመሰግነው አምላክ፣

በእግዚአብሔር ታምኛለሁ፤ አልፈራም፤

ሥጋ ለባሽ ምን ሊያደርገኝ ይችላል?

5ቀኑን ሙሉ ቃሌን ያጣምሙታል፤

ዘወትርም ሊጐዱኝ ያሤራሉ።

6ይዶልታሉ፤ ያደባሉ፤

ርምጃዬን ይከታተላሉ፤

ነፍሴንም ለማጥፋት ይሻሉ።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ ከቶ እንዳያመልጡ፣

ሕዝቦቹን በቍጣህ ጣላቸው።

8ሰቈቃዬን መዝግብ፤

እንባዬን በዕቃህ አጠራቅም፤56፥8 እንባዬን በወይን አቍማዳህ ውስጥ ጨምር ወይም እንባዬን በመጽሐፍህ መዝገብ

ሁሉስ በመዝገብህ የተያዘ አይደለምን?

9ወደ አንተ በተጣራሁ ቀን፣

ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው ይመለሳሉ፤

በዚህም፣ አምላክ ከጐኔ መቆሙን ዐውቃለሁ።

10ቃሉን በማመሰግነው አምላክ፣

ቃሉን በማመሰግነው በእግዚአብሔር

11በአምላክ ታምኛለሁ፤ አልፈራም፤

ሥጋ ለባሽ ምን ሊያደርገኝ ይችላል?

12እግዚአብሔር ሆይ፤ የአንተ ስእለት አለብኝ፤

የማቀርብልህም የምስጋና መሥዋዕት ነው፤

13በሕያዋን ብርሃን፣56፥13 ወይም በሕይወት ብርሃን

በእግዚአብሔር ፊት እመላለስ ዘንድ፣

ነፍሴን ከሞት፣56፥13 ወይም እኔን ከሞት

እግሬንም ከመሰናክል አድነሃልና።

Ketab El Hayat

مزمور 56:1-13

الْمَزْمُورُ السَّادِسُ وَالْخَمْسُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ عَلَى الْحَمَامَةِ الْبَكْمَاءِ فِي الأَمْاكِنِ الْبَعِيدَةِ. قَصِيدَةٌ ذَهَبِيَّةٌ لِدَاوُدَ عِنْدَمَا قَبَضَ عَلَيْهِ الْفِلِسْطِينِيُّونَ فِي جَتَّ

1ارْحَمْنِي يَا رَبُّ فَإِنَّ الإِنْسَانَ يَجِدُّ فِي مُطَارَدَتِي لاِفْتِرَاسِي. يُحَارِبُنِي الْيَوْمَ كُلَّهُ وَيُضَايِقُنِي. 2يَتَرَبَّصُ بِي أَعْدَائِي طَوَالَ الْيَوْمِ لاِبْتِلاعِي، وَمَا أَكْثَرَ الَّذِينَ يُحَارِبُونَنِي بِكِبْرِيَاءِ الْمُتَجَبِّرِينَ. 3فِي يَوْمِ خَوْفِي أَتَّكِلُ عَلَيْكَ. 4تَوَكَّلْتُ عَلَى اللهِ الَّذِي أَحْمَدُهُ عَلَى كَلامِهِ، فَلَا أَخَافُ. مَاذَا يَسْتَطِيعُ أَنْ يَصْنَعَ بِي الْبَشَرُ؟ 5يُحَرِّفُ أَعْدَائِي طَوَالَ الْيَوْمِ كَلامِي. كُلُّ أَفْكَارِهِمْ تَتَآمَرُ بِالشَّرِّ عَلَيَّ. 6يَتَجَمَّعُونَ عَلَيَّ وَيَكْمُنُونَ لِي. يَتَرَصَّدُونَ خُطْوَاتِي وَيَبْتَغُونَ نَفْسِي. 7عَاقِبْهُمْ يَا رَبُّ بِمُقْتَضَى إِثْمِهِمْ. أَخْضِعْ بِغَضَبِكَ الشُّعُوبَ يَا اللهُ. 8أَنْتَ رَاقَبْتَ تَشَرُّدِي. فَاحْفَظْ دُمُوعِي فِي خَزَانَتِكَ. أَمَا هِيَ فِي كِتَابِكَ؟

9عِنْدَمَا أَدْعُوكَ يَتَقَهْقَرُ أَعْدَائِي إِلَى الْوَرَاءِ. وَهَذَا مَا تَيَقَّنْتُ مِنْهُ: أَنَّ اللهَ مَعِي. 10أَحْمَدُ اللهَ عَلَى كَلامِهِ. أَحْمَدُ الرَّبَّ عَلَى كَلامِهِ. 11عَلَى اللهِ تَوَكَّلْتُ فَلَا أَخَافُ. مَاذَا يَسْتَطِيعُ أَنْ يَصْنَعَ بِي الإِنْسَانُ؟ 12يَا رَبُّ إِنِّي أُوْفِي مَا عَلَيَّ مِنْ نُذُورٍ، وَأُقَرِّبُ لَكَ ذَبَائِحَ الشُّكْرِ. 13لأَنَّكَ أَنْقَذْتَ نَفْسِي مِنَ الْمَوْتِ، وَحَفِظْتَ رِجْلَيَّ مِنَ الزَّلَقِ، لِكَيْ أَسْلُكَ أَمَامَ اللهِ فِي نُورِ الْحَيَاةِ.