መዝሙር 53 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 53:1-6

መዝሙር 53

አምላክ የለሾች

53፥1-6 ተጓ ምብ – መዝ 14፥1-7

ለመዘምራን አለቃ፤ በማኸላት፤ የዳዊት ትምህርት53 ርእሱ ምናልባት የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ቂል በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገርን የሚያደርግ አንድ እንኳ የለም።

2በማስተዋል የሚመላለስ፣

እግዚአብሔርን የሚፈልግ እንዳለ ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ

ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ወደ ሌላ ዘወር አሉ፤

በአንድነትም ተበላሹ፤

አንድ እንኳ

በጎ የሚያደርግ የለም።

4ሰው እንጀራ እንደሚበላ ሕዝቤን የሚበሉት፣

እግዚአብሔርንም ጠርተው የማያውቁት፣

እነዚያ ክፉ አድራጊዎች ከቶ አይማሩምን?

5የሚያስፈራ ነገር በሌለበት፣

በዚያ፣ በፍርሀት ተዋጡ፤

እግዚአብሔር የዘመቱብህን ሰዎች ዐጥንት በተነ፤

እርሱ እግዚአብሔር ስለ ናቃቸው፣ አንተ አሳፈርሃቸው።

6ምነው ለእስራኤል የሚሆን መዳን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ሐሤት ያድርግ፤ እስራኤል ደስ ይበለው።

Persian Contemporary Bible

مزامير 53:1-6

انسان بدكار

1كسی كه فكر می‌كند خدايی وجود ندارد، احمق است. چنين شخص فاسد است و دست به كارهای پليد می‌زند و هيچ نيكی در او نيست.

2خداوند از آسمان به انسانها نگاه می‌كند تا شخص فهميده‌ای بيابد كه طالب خدا باشد. 3اما همه از او روگردان شده‌اند، همه فاسد گشته‌اند و در وجود هيچيک از آنان نيكی نيست.

4اين بدكاران بی‌فهم خدا را نمی‌شناسند و قوم او را مانند نان می‌بلعند. 5ولی زمانی كه هيچ فكرش را نمی‌كنند ناگهان وحشت وجود آنها را فرا خواهد گرفت، زيرا خدا دشمنان قوم خود را هلاک كرده، استخوانهايشان را روی زمين پخش خواهد كرد. خدا آنان را طرد كرده است، بنابراين قوم او بر آنان چيره خواهند شد.

6قوم اسرائيل چقدر شاد خواهند شد وقتی خداوند آنان را رستگار و كامياب سازد! ای خداوند، از صهيون تجلی فرما و قوم خود را نجات ده!