መዝሙር 53 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 53:1-6

መዝሙር 53

አምላክ የለሾች

53፥1-6 ተጓ ምብ – መዝ 14፥1-7

ለመዘምራን አለቃ፤ በማኸላት፤ የዳዊት ትምህርት53 ርእሱ ምናልባት የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ቂል በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገርን የሚያደርግ አንድ እንኳ የለም።

2በማስተዋል የሚመላለስ፣

እግዚአብሔርን የሚፈልግ እንዳለ ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ

ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ወደ ሌላ ዘወር አሉ፤

በአንድነትም ተበላሹ፤

አንድ እንኳ

በጎ የሚያደርግ የለም።

4ሰው እንጀራ እንደሚበላ ሕዝቤን የሚበሉት፣

እግዚአብሔርንም ጠርተው የማያውቁት፣

እነዚያ ክፉ አድራጊዎች ከቶ አይማሩምን?

5የሚያስፈራ ነገር በሌለበት፣

በዚያ፣ በፍርሀት ተዋጡ፤

እግዚአብሔር የዘመቱብህን ሰዎች ዐጥንት በተነ፤

እርሱ እግዚአብሔር ስለ ናቃቸው፣ አንተ አሳፈርሃቸው።

6ምነው ለእስራኤል የሚሆን መዳን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ሐሤት ያድርግ፤ እስራኤል ደስ ይበለው።

New International Version

Psalms 53:1-6

Psalm 53In Hebrew texts 53:1-6 is numbered 53:2-7.

For the director of music. According to mahalath.Title: Probably a musical term A maskilTitle: Probably a literary or musical term of David.

1The fool says in his heart,

“There is no God.”

They are corrupt, and their ways are vile;

there is no one who does good.

2God looks down from heaven

on all mankind

to see if there are any who understand,

any who seek God.

3Everyone has turned away, all have become corrupt;

there is no one who does good,

not even one.

4Do all these evildoers know nothing?

They devour my people as though eating bread;

they never call on God.

5But there they are, overwhelmed with dread,

where there was nothing to dread.

God scattered the bones of those who attacked you;

you put them to shame, for God despised them.

6Oh, that salvation for Israel would come out of Zion!

When God restores his people,

let Jacob rejoice and Israel be glad!