መዝሙር 52 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 52:1-9

መዝሙር 52

የክፉዎች ዕጣ ፈንታ

ለመዘምራን አለቃ፤ ኤዶማዊው ዶይቅ ወደ ሳኦል መጥቶ፣ “ዳዊት ወደ አቢሜሌክ ቤት መጥቷል” ብሎ በነገረው ጊዜ፤ የዳዊት52 ርእሱ ምናልባት የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። ትምህርት።

1ኀያል ሆይ፤ በክፋት ለምን ትኵራራለህ?

አንተ በእግዚአብሔር ዐይን የተናቅህ፣

እንዴትስ ዘወትር ትታበያለህ?

2አንተ ማታለልን ሥራዬ ብለህ የያዝህ፤

አንደበትህ እንደ ሰላ ምላጭ፣

ጥፋትን ያውጠነጥናል።

3ከበጎ ነገር ይልቅ ክፋትን፣

እውነትን ከመናገር ይልቅ ሐሰትን ወደድህ። ሴላ

4አንተ አታላይ አንደበት ሆይ፤

ጐጂ ቃላትን ሁሉ ወደድህ!

5እግዚአብሔር ግን ለዘላለም

ያንኰታኵትሃል፤

ይነጥቅሃል፤ ከድንኳንህም መንጥቆ ያወጣሃል፤

ከሕያዋንም ምድር ይነቅልሃል። ሴላ

6ጻድቃን ይህን አይተው ይፈራሉ፤

እንዲህ እያሉም ይሥቁበታል፤

7“እግዚአብሔርን መጠጊያ ያላደረገ፣

ነገር ግን በሀብቱ ብዛት የተመካ፣

በክፋቱም የበረታ፣

ያ ሰው እነሆ!”

8እኔ ግን በእግዚአብሔር ቤት፣

እንደ ለመለመ የወይራ ዛፍ ነኝ፤

ከዘላለም እስከ ዘላለም፣

በእግዚአብሔር ምሕረት እታመናለሁ።

9ስላደረግኸው ነገር ለዘላለም አመሰግንሃለሁ፤

ስምህ መልካም ነውና፣ ስምህን ተስፋ አደርጋለሁ፤

በቅዱሳንም መካከል አመሰግንሃለሁ።

Ketab El Hayat

مزمور 52:1-9

الْمَزْمُورُ الثَّانِي وَالْخَمْسُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ تَعْلِيمِيٌّ لِدَاوُدَ عِنْدَمَا أَخْبَرَ دُوَاغُ شَاوُلَ بِذَهَابِ دَاوُدَ إِلَى بَيْتِ أَخِيمَالِكَ.

1لِمَاذَا تَتَفَاخَرُ بِالشَّرِّ أَيُّهَا الْجَبَّارُ؟ إِنَّ رَحْمَةَ اللهِ تَدُومُ الْيَوْمَ كُلَّهُ 2لِسَانُكَ يَخْتَرِعُ الْمَسَاوِئَ، وَيُمَارِسُ الْغِشَّ وَيَجْرَحُ كَالْمُوسَى الْمَسْنُونَةِ. 3أَحْبَبْتَ الشَّرَّ أَكْثَرَ مِنَ الْخَيْرِ، وَالْكَذِبَ أَكْثَرَ مِنَ الصِّدْقِ. 4أَحْبَبْتَ كُلَّ كَلامٍ مُهْلِكٍ أَيُّهَا اللِّسَانُ الْمُنَافِقُ. 5حَقّاً سَيُدَمِّرُكَ اللهُ إِلَى الأَبَدِ، وَيَخْتَطِفُكَ وَيَقْتَلِعُكَ مِنْ خَيْمَتِكَ، وَيَسْتَأْصِلُكَ مِنْ أَرْضِ الأَحْيَاءِ. 6فَيَرَى الأَبْرَارُ ذَلِكَ وَيَخَافُونَ؛ يَضْحَكُونَ عَلَيْكَ قَائِلِينَ: 7هَذَا هُوَ الرَّجُلُ الَّذِي لَمْ يَتَّخِذِ اللهَ حِصْناً لَهُ، بَلِ اتَّكَلَ عَلَى وَفْرَةِ غِنَاهُ وَاعْتَزَّ بِغِوَايَتِهِ.

8أَمَّا أَنَا فَمِثْلُ زَيْتُونَةٍ خَضْرَاءَ فِي بَيْتِ اللهِ وَثِقْتُ بِرَحْمَةِ اللهِ إِلَى الدَّهْرِ وَالأَبَدِ. 9أَحْمَدُكَ إِلَى الأَبَدِ عَلَى مَا فَعَلْتَ، وَأَنْتَظِرُ اسْمَكَ الصَّالِحَ فِي مَحْضَرِ أَتْقِيَائِكَ.