መዝሙር 5 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 5:1-12

መዝሙር 5

የጧት ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዘመር፣ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃሌን አድምጥ፤

መቃተቴንም ቸል አትበል።

2ንጉሤና አምላኬ ሆይ፤

ወደ አንተ እጸልያለሁና፣

ድረስልኝ ብዬ ስጮኽ ስማኝ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፤

በማለዳ ልመናዬን በፊትህ አቀርባለሁ፤

ፈቃድህንም በጥሞና እጠባበቃለሁ፤

4አንተ በክፋት ደስ የምትሰኝ አምላክ አይደለህም፤

ክፉም ከአንተ ጋር አያድርም።

5እብሪተኞች በፊትህ መቆም አይችሉም፤

ክፉ አድራጊዎችንም ሁሉ ጠላህ።

6ሐሰት የሚናገሩትን ታጠፋቸዋለህ፤

ደም የተጠሙትንና አታላዮችን፣

እግዚአብሔር ይጸየፋቸዋል።

7እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት

ወደ ቤትህ እገባለሁ፤

አንተንም በመፍራት፣

ወደ ተቀደሰው መቅደስህ እሰግዳለሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጠላቶቼ የተነሣ፣

በጽድቅህ ምራኝ፤

መንገድህንም በፊቴ አቅናልኝ።

9በንግግራቸው ውስጥ እውነት የለም፤

ልባቸው የጥፋት ጐሬ ነው፤

ጕረሯቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤

በምላሳቸውም ይሸነግላሉ።

10አምላክ ሆይ፤ የእጃቸውን ስጣቸው!

ተንኰላቸው መውደቂያቸው ይሁን፤

ከኀጢአታቸው ብዛት የተነሣ አስወግዳቸው፣

በአንተ ላይ ዐምፀዋልና።

11አንተን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ ግን ደስ ይበላቸው፤

ዘላለም በደስታ ይዘምሩ፤

ስምህን የሚወድዱ በአንተ ደስ እንዲላቸው፣

ተከላካይ ሁንላቸው።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቃንን ትባርካቸዋለህ፤

በሞገስህም እንደ ጋሻ ትከልላቸዋለህ።

Ketab El Hayat

مزمور 5:1-12

الْمَزْمُورُ الْخَامِسُ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ عَلَى آلاتِ النَّفْخِ مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1رَبُّ أَصْغِ إِلَى كَلامِي وَأَنْصِتْ إِلَى تَنَهُّدِي، 2اسْمَعْ إِلَى نِدَاءِ اسْتِغَاثَتِي يَا مَلِكِي وَإِلَهِي، فَإِنِّي إِلَيْكَ أُصَلِّي. 3فِي بَوَاكِيرِ الصَّبَاحِ تُصْغِي إِلَى صَوْتِي يَا رَبُّ، وَفِي الصَّبَاحِ أَتَوَجَّهُ إِلَيْكَ مُنْتَظِراً إِيَّاكَ. 4فَإِنَّكَ إِلَهٌ لَا يُسَرُّ بِالشَّرِّ. وَلَيْسَ لِلشِّرِّيرِ أَنْ يُقِيمَ فِي حَضْرَتِك. 5لَا يَمْثُلُ الْمُتَغَطْرِسُونَ أَمَامَكَ، فَإِنَّكَ تُبْغِضُ جَمِيعَ فَاعِلِي الإِثْمِ، 6وَتُهْلِكُ النَّاطِقِينَ بِالْكَذِبِ، لأَنَّكَ تَمْقُتُ سَافِكَ الدِّمَاءِ وَالْمَاكِرَ 7أَمَّا أَنَا فَبِفَضْلِ رَحْمَتِكَ الْعَظِيمَةِ أَدْخُلُ بَيْتَكَ. أَسْجُدُ فِي خُشُوعٍ وَرِعْدَةٍ فِي هَيْكَلِكَ الْمُقَدَّسِ.

8يَا رَبُّ أَرْشِدْنِي لِعَمَلِ بِرِّكَ عِنْدَ مُوَاجَهَةِ أَعْدَائِي لِي، وَسَهِّلْ أَمَامِي طَرِيقَكَ. 9إذْ لَيْسَ فِي أَفْوَاهِهِمْ صِدْقٌ وَدَاخِلُهُمْ مَفَاسِدُ، حَنَاجِرُهُمْ قُبُورٌ مَفْتُوحَةٌ وَأَلْسِنَتُهُمْ أَدَوَاتٌ لِلْمَكْرِ. 10احْكُمْ عَلَيْهِمِ اللهُمَّ، وَلْتَكُنْ مُؤَامَرَاتُهُمْ فَخّاً لَهُمْ يَسْقُطُونَ فِيهِ. طَوِّحْ بِهِمْ لِكَثْرَةِ مَعَاصِيهِمْ فَإِنَّهُمْ قَدْ تَمَرَّدُوا عَلَيْكَ.

11وَيَبْتَهِجُ جَمِيعُ الْمُتَّكِلِينَ عَلَيْكَ. إِلَى الأَبَدِ يَتَرَنَّمُونَ، لأَنَّكَ تُظَلِّلُهُمْ بِحِمَايَتِكَ، فَيَفْرَحُ بِكَ الَّذِينَ يُحِبُّونَ اسْمَكَ. 12لأَنَّكَ أَنْتَ يَا رَبُّ تُبَارِكُ الْبَارَّ وَتُطَوِّقُهُ بِتُرْسِ رِضَاكَ.