መዝሙር 49 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 49:1-20

መዝሙር 49

የሀብት ከንቱነት

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1እናንተ ሕዝቦች ሁላችሁ፤ ይህን ስሙ፤

በዓለም የምትኖሩ ሁሉ፤ ይህን አድምጡ።

2ዝቅተኞችና ከፍተኞች፤

ባለጠጎችና ድኾች ይህን በአንድነት ስሙ።

3አፌ የጥበብን ቃል ይናገራል፤

የልቤም ሐሳብ ማስተዋልን ይሰጣል።

4ጆሮዬን ወደ ምሳሌ አዘነብላለሁ፤

እንቆቅልሼንም በበገና እፈታለሁ።

5የአጭበርባሪዎች ክፋት በከበበኝ ጊዜ፣

በክፉ ቀን ለምን እፈራለሁ?

6በሀብታቸው የሚመኩትን፣

በብልጽግናቸውም የሚታመኑትን ለምን እፈራለሁ?

7የሌላውን ሕይወት መቤዠት የሚችል ሰው፣

ወይም ለእግዚአብሔር ወጆ የሚከፍልለት ማንም የለም።

8የነፍስ ቤዛ ውድ ነውና፤

በቂ ዋጋም ከቶ ሊገኝለት አይችልም፤

9በዚህም ዘላለም ይኖራል፣

መበስበስንም አያይም።

10ጠቢባን ሟቾች መሆናቸው የሚታይ ነው፤

ቂልና ሞኝም በአንድነት ይጠፋሉ፤

ጥሪታቸውንም ለሌላው ጥለው ይሄዳሉ።

11መሬቶችን በስማቸው ቢሰይሙም፣

መቃብራቸው የዘላለም ቤታቸው፣

ከትውልድ እስከ ትውልድም መኖሪያቸው ይሆናል።

12ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤

ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።49፥12 በሰብዓ ሊቃናት ትርጕምና በሱርስቱ ቅጅ 12 ከ20 ጋር አንድ ዐይነት ነው፤ ዕብራይስጡ ግን ከዚህ ይለያል።

13ይህ የተላላዎች ዕድል ፈንታ፣

የእነርሱንም አባባል ተቀብለው ለሚከተሏቸው፣

መጨረሻ ግብ ነው። ሴላ

14እንደ በጎች ለሲኦል49፥14 በዚህ እና በ15 ላይ ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቅጆች ግን መቃብር ይላሉ። የተዳረጉ ናቸው፤

ሞትም እረኛቸው ይሆናል፤

ቅኖች በማለዳ ይገዟቸዋል፤

አካላቸው ከክብር ቤታቸው ርቆ፣

በሲኦል ይፈራርሳል።

15እግዚአብሔር ግን ነፍሴን49፥15 ወይም ሕይወቴን ከሲኦል እጅ ይቤዣታል፤

በርግጥም በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት አለኝ። ሴላ

16ሰው ባለጠጋ ሲሆን፣

የቤቱም ክብር ሲበዛለት አትፍራ፤

17በሚሞትበትም ጊዜ ይዞት የሚሄደው አንዳች የለምና፤

ክብሩም አብሮት አይወርድም።

18በሕይወት ሳለ ራሱን እንደ ተባረከ ቢቈጥርም፣

ሰዎች በበለጸግህ ጊዜ ቢያወድሱህም፣

19ብርሃን ከቶ ወደማያዩት፣

ወደ አባቶች ማኅበር ይቀላቀላል።

20ሰው በሀብቱ እንደ ተከበረ አይዘልቅም፤

ታይተው የሚጠፉ እንስሳትን ይመስላል።

King James Version

Psalms 49:1-20

To the chief Musician, A Psalm for the sons of Korah.

1Hear this, all ye people; give ear, all ye inhabitants of the world:49.1 for: or, of

2Both low and high, rich and poor, together.

3My mouth shall speak of wisdom; and the meditation of my heart shall be of understanding.

4I will incline mine ear to a parable: I will open my dark saying upon the harp.

5Wherefore should I fear in the days of evil, when the iniquity of my heels shall compass me about?

6They that trust in their wealth, and boast themselves in the multitude of their riches;

7None of them can by any means redeem his brother, nor give to God a ransom for him:

8(For the redemption of their soul is precious, and it ceaseth for ever:)

9That he should still live for ever, and not see corruption.

10For he seeth that wise men die, likewise the fool and the brutish person perish, and leave their wealth to others.

11Their inward thought is, that their houses shall continue for ever, and their dwelling places to all generations; they call their lands after their own names.49.11 all…: Heb. generation and generation

12Nevertheless man being in honour abideth not: he is like the beasts that perish.

13This their way is their folly: yet their posterity approve their sayings. Selah.49.13 approve…: Heb. delight in their mouth

14Like sheep they are laid in the grave; death shall feed on them; and the upright shall have dominion over them in the morning; and their beauty shall consume in the grave from their dwelling.49.14 beauty: or, strength49.14 in the grave from…: or, the grave being an habitation to every one of them

15But God will redeem my soul from the power of the grave: for he shall receive me. Selah.49.15 power: Heb. hand49.15 the grave: or, hell

16Be not thou afraid when one is made rich, when the glory of his house is increased;

17For when he dieth he shall carry nothing away: his glory shall not descend after him.

18Though while he lived he blessed his soul: and men will praise thee, when thou doest well to thyself.49.18 while…: Heb. in his life

19He shall go to the generation of his fathers; they shall never see light.49.19 He…: Heb. The soul shall

20Man that is in honour, and understandeth not, is like the beasts that perish.