መዝሙር 47 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 47:1-9

መዝሙር 47

እግዚአብሔር፣ የእስራኤል ንጉሥና የዓለም ጌታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር።

1ሕዝቦች ሁላችሁ እጆቻችሁን አጨብጭቡ፤

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር እልል በሉ።

2በምድር ሁሉ ላይ ታላቅ የሆነው ንጉሥ፣

ልዑል እግዚአብሔር የሚያስፈራ ነውና።

3ሕዝቦችን ከእኛ በታች አደረገ፤

መንግሥታትንም ከእግራችን ሥር አስገዛልን።

4ለሚወድደው ለያዕቆብ ክብር የሆነችውን፣

ርስታችንን እርሱ መረጠልን። ሴላ

5አምላክ በእልልታ፣

እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።

6አምላካችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

ንጉሣችንን አወድሱት፤ አወድሱት፤

7እግዚአብሔር የምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና፤

ምርጥ ዝማሬ47፥7 ዕብራይስጡ ማስኪል ይላል፤ ይኸውም የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የሙዚቃውን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል። አቅርቡለት።

8እግዚአብሔር በሕዝቦች ላይ ነግሧል፤

እግዚአብሔር በተቀደሰ ዙፋኑ ላይ ተቀምጧል።

9ከአብርሃም አምላክ ሕዝብ ጋር፣

የሕዝቦች መኳንንት ተሰበሰቡ፤

የምድር ነገሥታት47፥9 ወይም ጋሾች የእግዚአብሔር ናቸውና፤

እርሱም እጅግ ከፍ ከፍ ያለ ነው።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 47:1-10

47

1さあ、皆さん、喜んで手をたたきましょう。

大声を上げて主をほめたたえましょう。

2このあらゆる神々にまさる主は、

ことばには尽くせないほど畏れかしこむべき方であり、

全地を治める偉大な王です。

3神は、私たちの下に国々を置いて治め、

4ご自分の愛する者たちに、

ご自身で最高の祝福を選んで与えてくださいます。

5鳴りわたるラッパの音と勇ましい雄叫びの中を、

神は昇って行かれました。

6-7私たちの主である神に向かって、

賛美の歌を高らかに歌いなさい。

全世界の王である神をほめ歌いなさい。

心からほめ歌いなさい。

8神は国々を治め、聖なる御座につかれます。

9全世界の支配者たちも、声を合わせて、

アブラハムの神をほめたたえました。

10諸国の勇者が手に取る盾は、

神の勝利のしるしです。

神は世界のどこででも

大きな栄誉をお受けになります。