መዝሙር 45 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 45:1-17

መዝሙር 45

የንጉሣዊ ሰርግ መዝሙር

ለመዘምራን አለቃ፤ “በጽጌረዳ” ዜማ፤ የቆሬ ልጆች ትምህርት፤ የፍቅር መዝሙር45 የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ልቤ መልካም ሐሳብ አፈለቀ፤

የተቀኘሁትን ቅኔ ለንጉሥ አሰማለሁ፤

አንደበቴም እንደ ባለሙያ ጸሓፊ ብርዕ ነው።

2አንተ ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ውብ ነህ፤

ከንፈሮችህም የጸጋ ቃል ያፈልቃሉ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ባርኮሃል።

3ኀያል ሆይ፤ ሰይፍህን በወገብህ ታጠቅ፤

ግርማ ሞገስንም ተላበስ።

4ስለ እውነት፣ ስለ ትሕትና፣ ስለ ጽድቅ

ሞገስን ተጐናጽፈህ በድል አድራጊነት ገሥግሥ፤

ቀኝ እጅህም ድንቅ ተግባር ታሳይ።

5የሾሉ ፍላጻዎችህ በንጉሥ ጠላቶች ልብ ይሰካሉ፤

ሕዝቦችም ከእግርህ በታች ይወድቃሉ።

6አምላክ ሆይ፤ ዙፋንህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይኖራል፤

የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ናት።

7ጽድቅን ወደድህ፤ ዐመፃን ጠላህ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ፣

ከጓደኞችህ ይልቅ አንተን የደስታ ዘይት ቀባህ።

8ልብስህ ሁሉ በከርቤ፣ በአደስና በጥንጁት መዐዛ ያውዳል፤

በዝኆን ጥርስ ከተዋቡ ቤተ መንግሥቶችም፣

የበገናና የመሰንቆ ድምፅ ደስ ያሰኙሃል።

9ከተከበሩት ሴቶችህ መካከል የነገሥታት ሴቶች ልጆች ይገኛሉ፤

ንግሥቲቱም በኦፊር ወርቅ አጊጣ በቀኝህ ቆማለች።

10ልጄ ሆይ፤ አድምጪ፤ አስተውዪ፤ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤

ሕዝብሽንና የአባትሽን ቤት እርሺ።

11ንጉሥ በውበትሽ ተማርኳል፤

ጌታሽ ነውና አክብሪው።

12የጢሮስ ሴት ልጅ እጅ መንሻ ይዛ ትመጣለች፤45፥12 ወይም፣ የጢሮሳውያን ልብሰ ተክህኖ ከስጦታዎቹ መካከል አለ

ሀብታሞችም ደጅ ይጠኑሻል።

13የንጉሥ ልጅ ከላይ እስከ ታች ተሸልማ እልፍኟ ውስጥ አለች፤

ልብሷም ወርቀ ዘቦ ነው።

14በጥልፍ ሥራ ባጌጠ ልብስ ወደ ንጉሥ ትወሰዳለች፤

ደናግል ጓደኞቿም ተከትለዋት፣

ወደ አንተ ይመጣሉ።

15በደስታና በሐሤት ወደ ውስጥ ይመሯቸዋል፤

ወደ ንጉሡም ቤተ መንግሥት ይገባሉ።

16ወንዶች ልጆችህ በአባቶችህ እግር ይተካሉ፤

ገዦችም አድርገሽ በምድር ሁሉ ትሾሚያቸዋለሽ።

17ስምሽን በትውልድ ሁሉ ዘንድ መታሰቢያ አደርጋለሁ፤

ስለዚህ ሕዝቦች ከዘላለም እስከ ዘላለም ያወድሱሃል።

New International Version

Psalms 45:1-17

Psalm 45In Hebrew texts 45:1-17 is numbered 45:2-18.

For the director of music. To the tune of “Lilies.” Of the Sons of Korah. A maskil.Title: Probably a literary or musical term A wedding song.

1My heart is stirred by a noble theme

as I recite my verses for the king;

my tongue is the pen of a skillful writer.

2You are the most excellent of men

and your lips have been anointed with grace,

since God has blessed you forever.

3Gird your sword on your side, you mighty one;

clothe yourself with splendor and majesty.

4In your majesty ride forth victoriously

in the cause of truth, humility and justice;

let your right hand achieve awesome deeds.

5Let your sharp arrows pierce the hearts of the king’s enemies;

let the nations fall beneath your feet.

6Your throne, O God,45:6 Here the king is addressed as God’s representative. will last for ever and ever;

a scepter of justice will be the scepter of your kingdom.

7You love righteousness and hate wickedness;

therefore God, your God, has set you above your companions

by anointing you with the oil of joy.

8All your robes are fragrant with myrrh and aloes and cassia;

from palaces adorned with ivory

the music of the strings makes you glad.

9Daughters of kings are among your honored women;

at your right hand is the royal bride in gold of Ophir.

10Listen, daughter, and pay careful attention:

Forget your people and your father’s house.

11Let the king be enthralled by your beauty;

honor him, for he is your lord.

12The city of Tyre will come with a gift,45:12 Or A Tyrian robe is among the gifts

people of wealth will seek your favor.

13All glorious is the princess within her chamber;

her gown is interwoven with gold.

14In embroidered garments she is led to the king;

her virgin companions follow her—

those brought to be with her.

15Led in with joy and gladness,

they enter the palace of the king.

16Your sons will take the place of your fathers;

you will make them princes throughout the land.

17I will perpetuate your memory through all generations;

therefore the nations will praise you for ever and ever.