መዝሙር 41 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 41:1-13

መዝሙር 41

የሕመምተኛና የብቸኛ ሰው ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ለድኾች የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው፤

እርሱንም እግዚአብሔር በክፉ ቀን ይታደገዋል።

2እግዚአብሔር ይጠብቀዋል፤ በሕይወትም ያኖረዋል፤

በምድርም ላይ ይባርከዋል፤

ለጠላቶቹም ምኞት አሳልፎ አይሰጠውም።

3ታሞ ባለበት ዐልጋ ላይ እግዚአብሔር ይንከባከበዋል፤

በበሽታውም ጊዜ መኝታውን ያነጥፍለታል።

4እኔም፣ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረት አድርግልኝ፤

አንተን በድያለሁና ነፍሴን ፈውሳት” አልሁ።

5ጠላቶቼ በክፋት በመናገር፣ “የሚሞተው መቼ ነው? ስሙስ

የሚደመሰሰው ምን ቀን ነው?” ይላሉ።

6ሊጠይቀኝ የሚመጣ ቢኖር፣

በልቡ ስድብ እያጠራቀመ፣ ከዐንገት በላይ ይናገራል፤

ወጥቶም ወሬ ይነዛል።

7ጠላቶቼ ሁሉ ግንባር ፈጥረው ይንሾካሾኩብኛል፤

እንዲህ እያሉም፣

የከፋ ነገር በላዬ ያውጠነጥናሉ፤

8“ክፉ ደዌ ይዞታል፤

ከእንግዲህም ከተኛበት አይነሣም።”

9እንጀራዬን ተካፍሎኝ የበላ፣

የምተማመንበትም የቅርብ ወዳጄ፣

በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣ።

10እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ምሕረት አድርግልኝ፤

የእጃቸውን እንድከፍላቸው አስነሣኝ።

11ጠላቴ በላዬ ድል አላገኘምና፣

እንደ ወደድኸኝ በዚህ ዐወቅሁ።

12ስለ ጭንቀቴ ደግፈህ ይዘኸኛል፤

በፊትህም ለዘላለም ታኖረኛለህ።

13የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር

ከዘላለም እስከ ዘላለም የተባረከ ይሁን፤

አሜን፤ አሜን።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 41:1-13

41

1貧しい者に親切な人は、神から祝福を受けます。

その人が困難に会うとき、

主は助けの手を差し伸べてくださいます。

2その人を無事に守って生かし、

人前で面目を施させ、敵を散らしてくださいます。

3病気のときは、主ご自身が看護に当たり、

痛みをやわらげ、心配事を取り去ってくださるのです。

4私はこう祈りました。

「ああ主よ、私をあわれんで、病気を治してください。

私は罪を洗いざらい告白したのですから。」

5ところが敵は、

「さっさと死んで、忘れ去られてしまえばよい」

と言っています。

6彼らは、いかにも親しげに病床の私を見舞いますが、

心の中では憎悪をたぎらせ、

私が苦しみの床に伏している姿を見て

ほくそ笑むのです。

一歩外に出ると、大笑いし、あざけり、

7私が死んだら何をしようかと、

ひそひそ耳打ちし合っています。

8彼らはこう言います。

「どんな病気か知らないが、もうすぐおしまいだ。

二度と起き上がれるものか。」

9食事を共にした親友さえ、私を裏切りました。

10主よ、どうか私を見殺しにしないでください。

あわれんでください。どうか健康な体に戻し、

彼らを見返すことができるようにしてください。

11あなたは、敵が私に勝ち誇ることを

お許しになりませんでした。

私は自分が神の御目に

かなっていることを知りました。

12私が正直に生きてきたからこそ、

あなたはこれまで守ってくださったのです。

これから先、いつまでも目をかけてくださいます。

13イスラエルの神である主をあがめよう。

この方は永遠に生きておられます。

アーメン。アーメン。