መዝሙር 34 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 34:1-22

መዝሙር 3434 34 የዚህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀመር ሲሆን፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

የእግዚአብሔር ፍትሕ ውዳሴ

እንደ እብድ ሆኖ አቤሜሌክ ፊት በመቅረቡ ተባርሮ በወጣ ጊዜ የዘመረው፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እባርከዋለሁ፤

ምስጋናውም ዘወትር ከአፌ አይለይም።

2ነፍሴ በእግዚአብሔር ተመካች፤

ትሑታንም ይህን ሰምተው ሐሤት ያደርጋሉ።

3ኑና ከእኔ ጋር እግዚአብሔርን አክብሩት፤

ስሙንም በአንድነት ከፍ ከፍ እናድርግ።

4እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤ እርሱም መለሰልኝ፤

ከፍርሀቴም ሁሉ አዳነኝ።

5ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤

ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።

6ይህ ችግረኛ ጮኸ፤ እግዚአብሔርም ሰማው፤

ከመከራውም ሁሉ አዳነው።

7እግዚአብሔርን በሚፈሩት ዙሪያ የእግዚአብሔር መልአክ ይሰፍራል፤

ያድናቸዋልም።

8እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እዩ፤

እርሱን መጠጊያ የሚያደርግ ምንኛ ቡሩክ ነው!

9እናንተ ቅዱሳኑ፤ እግዚአብሔርን ፍሩት፤

እርሱን የሚፈሩት አንዳች አያጡምና።

10አንበሶች ሊያጡ፣ ሊራቡም ይችላሉ፤

እግዚአብሔርን የሚሹ ግን መልካም ነገር አይጐድልባቸውም።

11ልጆቼ ሆይ፣ ኑ፤ ስሙኝ፤

እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ።

12ሕይወትን የሚወድድ፣

በጎውንም ያይ ዘንድ ዕድሜን የሚመኝ ማን ነው?

13አንደበትህን ከክፉ ነገር ከልክል፤

ከንፈርህንም ከሽንገላ ጠብቅ።

14ከክፉ ሽሽ፤ መልካሙንም አድርግ፤

ሰላምን ፈልጋት፤ ተከተላትም።

15የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ናቸው፤

ጆሮዎቹም ለጩኸታቸው ክፍት ናቸው።

16መታሰቢያቸውን ከምድር ለማጥፋት፣

የእግዚአብሔር ፊት በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።

17ጻድቃን ሲጮኹ፣ እግዚአብሔር ይሰማቸዋል፤

ከመከራቸውም ሁሉ ያድናቸዋል።

18እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፤

መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።

19የጻድቅ መከራው ብዙ ነው፤

እግዚአብሔር ግን ከሁሉም ያድነዋል።

20ዐጥንቶቹን ሁሉ ይጠብቃል፤

ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።

21ኀጢአተኞችን ክፋት ይገድላቸዋል፤

ጻድቃንን የሚጠሉ ይፈረድባቸዋል።

22እግዚአብሔር የባሪያዎቹን ነፍስ ይቤዣል፤

እርሱንም መጠጊያ ያደረገ አይፈረድበትም።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 34:1-22

第 34 篇

上帝的美善

大卫在亚比米勒面前装疯,被赶出去后,作了此诗。

1我要常常称颂耶和华,

时刻赞美祂。

2我要夸耀祂的作为,

困苦人听见必欢欣。

3让我们一同颂赞祂的伟大,

尊崇祂的名!

4我向祂祷告,祂便应允我,

救我脱离一切恐惧。

5凡仰望祂的必有荣光,

不致蒙羞。

6我这可怜的人向祂呼求,

祂就垂听,

救我脱离一切困境。

7祂的天使必四面保护敬畏祂的人,拯救他们。

8你们要亲身体验,

就知道耶和华的美善;

投靠祂的人有福了!

9耶和华的圣民啊,

你们要敬畏祂,

因为敬畏祂的人一无所缺。

10壮狮也会忍饥挨饿,

但寻求耶和华的人什么福分都不缺。

11孩子们啊,听我说,

我要教导你们敬畏耶和华。

12若有人热爱生命,

渴望长寿和幸福,

13就要舌头不出恶言,

嘴唇不说诡诈的话。

14要弃恶行善,

竭力追求和睦。

15耶和华的眼睛看顾义人,

祂的耳朵垂听他们的呼求。

16耶和华严惩作恶之人,

从世上铲除他们。

17义人向耶和华呼救,祂就垂听,

拯救他们脱离一切患难。

18祂安慰悲痛欲绝的人,

拯救心灵破碎的人。

19义人也会遭遇许多患难,

但耶和华必拯救他,

20保全他一身的骨头,

连一根也不折断。

21恶人必遭恶报,

与义人为敌的必被定罪。

22耶和华必救赎祂的仆人,

投靠祂的人必不被定罪。