መዝሙር 30 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 30:1-12

መዝሙር 30

ከክፉ አደጋ የዳነ ሰው ምስጋና

ለቤተ መቅደሱ ምረቃ የተዘመረ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ከታች አንሥተኸኛልና፣

ጠላቶቼም በላዬ እንዳይደሰቱ አድርገሃልና፣

ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።

2እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ትረዳኝ ዘንድ ወደ አንተ ጮኽሁ፤

አንተም ፈወስኸኝ።

3እግዚአብሔር ሆይ ነፍሴን ከሲኦል30፥3 ወይም ከመቃብር አወጣሃት፤

ወደ ጕድጓድ ከመውረድም መልሰህ ሕያው አደረግኸኝ።

4እናንተ ቅዱሳኑ፤ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤

ቅዱስ ስሙንም አወድሱ።

5ቍጣው ለዐጭር ጊዜ ነው፤

ቸርነቱ ግን እስከ ዕድሜ ልክ ነውና፤

ሌሊቱን በልቅሶ ቢታደርም፣

በማለዳ ደስታ ይመጣል።

6እኔም በተረጋጋሁ ጊዜ፣

“ከቶ አልናወጥም” አልሁ።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ በአንተ ሞገስ፣

ተራሮቼ30፥7 ወይም ኰረብታማ የሆነች አገሬ ጸኑ፣

ፊትህን በሰወርህ ጊዜ ግን፣

ውስጤ ታወከ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ ተጣራሁ፤

ወደ ጌታም እንዲህ ብዬ ጮኽሁ፤

9“በእኔ ወደ ጕድጓድ መውረድ፣

በመሞቴ ምን ጥቅም ይገኛል?30፥9 ወይም ዝም ብል…ይገኛል?

ዐፈር ያመሰግንሃልን?

ታማኝነትህንስ ይናገራልን?

10እግዚአብሔር ሆይ፤ ስማ፤ ማረኝም፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ረዳት ሁነኝ።”

11ዋይታዬን ወደ ሽብሸባ ለወጥህልኝ፤

ማቄን አውልቀህ ፍሥሓን አለበስኸኝ፤

12እንግዲህ ነፍሴ ታመስግንህ፤ ዝምም አትበል፤

እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ለዘላለም አመሰግንሃለሁ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 30:1-12

30

1私は主をほめたたえます。

神は私を敵の手から助け出し、

敵が勝ち誇るのをお許しにならなかったからです。

2ああ主よ。主は私の願いを聞き入れて、

元の健康な体に戻してくださいました。

3墓の入口から、連れ戻してくださいました。

おかげで、こうして生きることができます。

4主を信じる人よ。主を賛美し、

主のきよい御名に感謝しなさい。

5主の怒りはつかの間ですが、

その恵みは生きる限り続きます。

たとえ、夜通し泣き明かすことがあっても、

朝には喜びが訪れます。

6-7順境の日に、私は言いました。

「いつまでも今のままだ。

だれも私のじゃまはできない。

主が恵んでくださって、

私をびくともしない山のようにしてくださった。」

ところが、神は顔をそむけて、

祝福の川をからしたのです。

たちまち私は意気消沈し、恐怖におびえました。

8ああ主よ。私は大声でお願いしました。

9「主よ、私を殺したって、一文の得にもなりません。

生きていてこそ、友人の前で

あなたをたたえることができるのです。

墓に埋められたら、どうしてあなたの真実を

世間に知らせることができましょう。

10ああ主よ、どうか私をあわれみ、助けてください。」

11すると、神は嘆きを喜びに変え、喪服を脱がせて、

きらびやかな晴れ着を着せてくださいました。

12墓に埋められることなく、

神に喜ばしい賛美の歌声を上げるためです。

ああ神、主よ。

私はいつまでもこの感謝の気持ちを忘れません。