መዝሙር 25 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 25:1-22

መዝሙር 2525 ይህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

በዐደጋ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁ፤

2አምላኬ ሆይ፣ በአንተ እታመናለሁ፤

እባክህ አታሳፍረኝ፤

ጠላቶቼም አይዘባነኑብኝ።

3አንተን ተስፋ የሚያደርጉ፣

ከቶ አያፍሩም፤

ነገር ግን እንዲያው ያለ ምክንያት፣

ተንኰለኞች የሆኑ ያፍራሉ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ አካሄድህን እንዳውቅ አድርገኝ፤

መንገድህንም አስተምረኝ።

5አንተ አዳኜ፣ አምላኬም ነህና፣

በእውነትህ ምራኝ፤ አስተምረኝም፤

ቀኑን ሙሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።

6እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህንና ፍቅርህን ዐስብ፤

እነዚህ ከጥንት የነበሩ ናቸውና።

7የልጅነቴን ኀጢአት፣

መተላለፌንም አታስብብኝ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ ብዛት፣

እንደ ምሕረትህም መጠን አስበኝ።

8እግዚአብሔር መልካምና ቅን ነው፤

ስለዚህ ኀጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።

9ዝቅ ያሉትን በፍትሕ ይመራቸዋል፤

ለትሑታንም መንገዱን ያስተምራቸዋል።

10ኪዳኑንና ሥርዐቱን ለሚጠብቁ፣

የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ናቸው።

11እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአቴ ታላቅ ነውና፣

ስለ ስምህ ይቅር በልልኝ።

12እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው?

በተመረጠለት መንገድ ያስተምረዋል።

13ዘመኑን በተድላ ደስታ ያሳልፋል፤

ዘሩም ምድርን ይወርሳል።

14እግዚአብሔር ምስጢሩን ከሚፈሩት ወዳጆቹ አይሰውርም፤

ኪዳኑንም ይገልጥላቸዋል።

15ዐይኖቼ ሁልጊዜ ወደ እግዚአብሔር ናቸው፤

እግሮቼን ከወጥመድ የሚያላቅቃቸው እርሱ ነውና።

16እኔ ብቸኛና የተጨነቅሁ እንደ መሆኔ፣

ወደ እኔ ተመለስ፤ ምሕረትም አድርግልኝ።

17የልቤ መከራ በዝቷል፤

ከጭንቀቴ ገላግለኝ።

18ጭንቀቴንና መከራዬን ተመልከት፤

ኀጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ።

19ጠላቶቼ እንዴት እንደ በዙ ተመልከት፤

እንዴት አምርረው እንደሚጠሉኝ እይ።

20ነፍሴን ጠብቃት፤ ታደገኝም፤

መጠጊያዬ ነህና አታሳፍረኝ።

21አንተን ተስፋ አድርጌአለሁና፣

ታማኝነትና ቅንነት ይጠብቁኝ።

22አምላክ ሆይ፤ እስራኤልን

ከመከራው ሁሉ አድነው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 25:1-22

第 25 篇

祈求引導和赦免

大衛的詩。

1耶和華啊,我的心仰望你。

2我的上帝啊,我信靠你,

求你不要叫我蒙羞,

不要讓我的仇敵勝過我。

3信靠你的必不羞愧,

背信棄義者必蒙羞。

4耶和華啊,

求你指引我走你的路,

教導我行你的道。

5求你以你的真理引領我,

教導我,因為你是拯救我的上帝,

我日夜仰望你。

6耶和華啊,

求你顧念你亙古以來常施的憐憫和慈愛,

7求你饒恕我年輕時的罪惡和過犯,

以你的恩惠和慈愛待我。

8耶和華良善公正,

祂教導罪人走正路,

9指引謙卑人追求公義,

教導他們行祂的道。

10遵守祂的約和法度的人,

耶和華以慈愛和信實相待。

11耶和華啊,我罪惡深重,

求你為了自己的名而赦免我。

12凡敬畏耶和華的人,

耶和華必指示他當走的路。

13他必享福,

他的後代必承受土地。

14耶和華與敬畏祂的人為友,

使他們認識祂的約。

15我常常仰望耶和華,

因為唯有祂能救我脫離網羅。

16耶和華啊,我孤苦零丁,

求你眷顧我,恩待我。

17我心中充滿愁煩,

求你救我脫離患難。

18求你體恤我的憂傷和痛苦,

赦免我的罪惡。

19看啊,我的仇敵眾多,

他們都痛恨我。

20求你保護、搭救我的性命,

別讓我蒙羞,因為我投靠你。

21求你以誠實和正義護衛我,

因為我仰望你。

22上帝啊,

求你救贖以色列脫離一切困境。