መዝሙር 2 – NASV & KLB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 2:1-12

መዝሙር 2

መሲሓዊ ትዕይንት

1ሕዝቦች ለምን ያሤራሉ?2፥1 ዕብራይስጡ እንዲሁ ሲሆን፣ ሰብዓ ሊቃናት ግን ይቈጣሉ ይላል።

ሰዎችስ ለምን ከንቱ ነገር ያውጠነጥናሉ?

2የምድር ነገሥታት ተነሡ፤

ገዦችም በእግዚአብሔርና በመሲሑ2፥2 ወይም የተቀባው ላይ

ሊመክሩ ተሰበሰቡ፤

3“ሰንሰለታቸውን እንበጥስ፣

የእግር ብረታቸውንም አውልቀን እንጣል” አሉ።

4በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጠው ይሥቃል፤

ጌታም ይሣለቅባቸዋል።

5ከዚያም በቍጣው ይናገራቸዋል፤

በመዓቱም ያስደነግጣቸዋል፤

6ደግሞም፣ “እኔ ግን በተቀደሰው ተራራዬ፣

በጽዮን ላይ የራሴን ንጉሥ ሾምሁ” ይላል።

7የእግዚአብሔርን ሕግ ዐውጃለሁ፤

እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “አንተ ልጄ ነህ፤

እኔ ዛሬ ወለድሁህ፤2፥7 ወይም …አባትህ ሆንሁ

8ለምነኝ፤

መንግሥታትን ርስት አድርጌ፣

የምድርንም ዳርቻ ግዛት እንዲሆንህ እሰጥሃለሁ።

9አንተም በብረት በትር ትቀጠቅጣቸዋለህ፤2፥9 ወይም በብረት ዘንግ ትሰባብራቸዋለህ

እንደ ሸክላ ዕቃ ታደቅቃቸዋለህ።”

10ስለዚህ እናንት ነገሥታት ልብ በሉ፤

እናንት የምድር ገዦችም፣ ተጠንቀቁ።

11እግዚአብሔርን በፍርሀት አገልግሉት፤

ለእርሱ መራድም ደስ ያሰኛችሁ።

12እንዳይቈጣና በመንገድ እንዳትጠፉ፣

ዝቅ ብላችሁ ልጁን ሳሙት፤

ቍጣው ፈጥኖ ይነድዳልና።

እርሱን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ የተባረኩ ናቸው።

Korean Living Bible

시편 2:1-12

메시아의 승리와 그의 왕국

1어째서 이방 나라들이

떠들어대며 민족들이

헛된 일을 꾸미는가?

2세상의 왕들이 들고 일어나며

지도자들이 함께 모여

여호와와 그의 기름 부은 자를

대적하여

3“자, 우리가

2:3 원문에는 ‘그들의’그의 사슬을 끊어 버리고

그의 속박에서

벗어나자” 하는구나.

4하늘에 계신 여호와께서 웃으시며

그들을 비웃으신다.

5그러고서 분노하사

그들을 꾸짖고 놀라게 하시며

6“내가 나의 거룩한 산 시온에

내 왕을 세웠다” 하시는구나.

72:7 암시됨.여호와께서 택하신 왕이

대답하신다.

“여호와께서 선포하신 것을

내가 알리노라.

그가 나에게 말씀하셨다.

‘너는 내 아들이다.

오늘 내가 너를 낳았다.

8나에게 구하라.

내가 모든 나라를 너에게 줄 것이니

온 세상이 네 소유가 되리라.

9네가 쇠막대기로 그들을 다스리며

질그릇같이 부숴 버릴 것이다.’ ”

10세상의 왕들과 지도자들아,

이제 너희는 이 경고를 듣고

교훈을 얻어라.

11여호와를 두려운 마음으로 섬기고

떨며 즐거워하여라.

12그 아들에게 입맞추어라.

그렇지 않으면

그의 분노가 순식간에 터져

너희가 망할 것이다.

여호와를 의지하는 자는

복이 있으리라.