መዝሙር 147 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 147:1-20

መዝሙር 147

መዝሙር ለሁሉን ቻይ አምላክ

1ሃሌ ሉያ።147፥1 አንዳንዶች ከ20 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

አምላካችንን በመዝሙር ማወደስ እንዴት መልካም ነው!

እርሱን ማመስገን ደስ ያሰኛል፤ ይህ ተገቢም ነው።

2እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን መልሶ ይሠራታል፤

ከእስራኤል የተበተኑትን ይሰበስባል።

3ልባቸው የተሰበረውን ይፈውሳል፤

ቍስላቸውንም ይጠግናል።

4የከዋክብትን ብዛት ያውቃል፤

እያንዳንዱንም በስሙ ይጠራዋል።

5ጌታችን ታላቅ ነው፤ እጅግ ኀያልም ነው፤

ለጥበቡም ወሰን የለውም።

6እግዚአብሔር ትሑታንን ከፍ ያደርጋል፤

ክፉዎችን ግን ወደ ምድር ይጥላል።

7ለእግዚአብሔር በምስጋና ዘምሩ፤

ለአምላካችንም በመሰንቆ ምስጋና አቅርቡ።

8ሰማይን በደመናት የሚሸፍን እርሱ ነው፤

ለምድርም ዝናብን ይሰጣል፤

በተራሮችም ላይ ሣር ያበቅላል።

9ለእንስሳት ምግባቸውን፣

የቍራ ጫጩቶችም ሲንጫጩ የሚበሉትን ይሰጣቸዋል።

10እርሱ በፈረስ ኀይል አይደሰትም፤

በሯጭም ብርታት ላይ ደስታውን አያደርግም።

11ነገር ግን እግዚአብሔር በሚፈሩት፣

በምሕረቱ በሚታመኑትም ይደሰታል።

12ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግዚአብሔርን አመስግኚ፤

ጽዮን ሆይ፤ አምላክሽን አወድሺ፤

13እርሱ የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቷልና፤

ልጆችሽንም በውስጥሽ ባርኳል።

14በድንበርሽ ውስጥ ሰላም ያሰፍናል፤

ማለፊያ ስንዴም ያጠግብሻል።

15ትእዛዙን ወደ ምድር ይልካል፤

ቃሉም እጅግ በፍጥነት ይሮጣል።

16ዐመዳዩን እንደ በርኖስ ይዘረጋል፤

ውርጩን እንደ ዐመድ ይነሰንሳል።

17የበረዶውን ድንጋይ ቍልቍል ይወረውረዋል፤

በውሽንፍሩስ ቅዝቃዜ ፊት ማን ሊቆም ይችላል?

18ቃሉን ልኮ ያቀልጣቸዋል፤ ነፋሱን ያነፍሳል፤ ውሆችንም ያፈስሳል።

19ቃሉን ለያዕቆብ፣

ሥርዐቱንና ፍርዱን ለእስራኤል ይገልጣል።

20ይህን ለማንኛውም ሌላ ሕዝብ አላደረገም፤

እነርሱም ፍርዱን አላወቁም።

ሃሌ ሉያ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 147:1-20

147

1ハレルヤ。主をほめたたえましょう。

神を賛美するのは、なんと麗しく、

喜ばしいことなのでしょう。

2主はエルサレムの町を建て直し、

捕虜として連れ去られた人々を返してくださいます。

3心の傷ついた人々を優しくいたわり、

傷口を覆ってくださいます。

4主は星を数え、その一つ一つの名を呼ばれます。

5偉大な主の御力は限りなく、主の知恵は無限です。

6主は謙遜な人を支えますが、

悪者どもは地面に倒されます。

7主に感謝の歌を歌いなさい。

竪琴の伴奏で、賛美の歌を歌いなさい。

8神は雲で天を覆い隠し、夕立を送り、

牧草を青々と生えさせてくださいます。

9また野の獣を養われます。

からすの子は、神に食べ物をねだって鳴くのです。

10どんなに足の早い馬でも、

神から見れば、歩みの遅いかたつむりと同じです。

どんなに腕力を誇る人でも、神からすれば、

赤ん坊の手をねじ伏せるより簡単なのです。

11しかし、主を敬い、その愛と恵みを待ち望む人々を、

主はことのほかお喜びになります。

12エルサレムは主をほめたたえなさい。

シオンも賛美の声を上げなさい。

13主は敵に備えてあなたの城の守りを固め、

あなたの子どもたちを祝福されるからです。

14主は平和を与え、

最上の小麦で倉を満たしてくださいます。

15主のご命令は全世界に行き渡ります。

そのおことばは、飛ぶように駆け巡るのです。

16主は真っ白な雪を降らせ、地面に霜をまき、

17雹を地上に投げつけられます。

その凍りつくような寒さに、だれが耐えられましょう。

18しかし、主が春をお呼びになると、

暖かい風が吹いてきて、川面の氷を溶かすのです。

19主はイスラエルに、

ご自分のおきてと礼拝の仕方を教えてくださいました。

20こんなことは、ほかの国にはなかったことです。

他の国民は、神の戒めを聞かされていません。

ハレルヤ。主をほめたたえましょう。