መዝሙር 147 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 147:1-20

መዝሙር 147

መዝሙር ለሁሉን ቻይ አምላክ

1ሃሌ ሉያ።147፥1 አንዳንዶች ከ20 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

አምላካችንን በመዝሙር ማወደስ እንዴት መልካም ነው!

እርሱን ማመስገን ደስ ያሰኛል፤ ይህ ተገቢም ነው።

2እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን መልሶ ይሠራታል፤

ከእስራኤል የተበተኑትን ይሰበስባል።

3ልባቸው የተሰበረውን ይፈውሳል፤

ቍስላቸውንም ይጠግናል።

4የከዋክብትን ብዛት ያውቃል፤

እያንዳንዱንም በስሙ ይጠራዋል።

5ጌታችን ታላቅ ነው፤ እጅግ ኀያልም ነው፤

ለጥበቡም ወሰን የለውም።

6እግዚአብሔር ትሑታንን ከፍ ያደርጋል፤

ክፉዎችን ግን ወደ ምድር ይጥላል።

7ለእግዚአብሔር በምስጋና ዘምሩ፤

ለአምላካችንም በመሰንቆ ምስጋና አቅርቡ።

8ሰማይን በደመናት የሚሸፍን እርሱ ነው፤

ለምድርም ዝናብን ይሰጣል፤

በተራሮችም ላይ ሣር ያበቅላል።

9ለእንስሳት ምግባቸውን፣

የቍራ ጫጩቶችም ሲንጫጩ የሚበሉትን ይሰጣቸዋል።

10እርሱ በፈረስ ኀይል አይደሰትም፤

በሯጭም ብርታት ላይ ደስታውን አያደርግም።

11ነገር ግን እግዚአብሔር በሚፈሩት፣

በምሕረቱ በሚታመኑትም ይደሰታል።

12ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግዚአብሔርን አመስግኚ፤

ጽዮን ሆይ፤ አምላክሽን አወድሺ፤

13እርሱ የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቷልና፤

ልጆችሽንም በውስጥሽ ባርኳል።

14በድንበርሽ ውስጥ ሰላም ያሰፍናል፤

ማለፊያ ስንዴም ያጠግብሻል።

15ትእዛዙን ወደ ምድር ይልካል፤

ቃሉም እጅግ በፍጥነት ይሮጣል።

16ዐመዳዩን እንደ በርኖስ ይዘረጋል፤

ውርጩን እንደ ዐመድ ይነሰንሳል።

17የበረዶውን ድንጋይ ቍልቍል ይወረውረዋል፤

በውሽንፍሩስ ቅዝቃዜ ፊት ማን ሊቆም ይችላል?

18ቃሉን ልኮ ያቀልጣቸዋል፤ ነፋሱን ያነፍሳል፤ ውሆችንም ያፈስሳል።

19ቃሉን ለያዕቆብ፣

ሥርዐቱንና ፍርዱን ለእስራኤል ይገልጣል።

20ይህን ለማንኛውም ሌላ ሕዝብ አላደረገም፤

እነርሱም ፍርዱን አላወቁም።

ሃሌ ሉያ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 147:1-20

第 147 篇

讚美上帝復興耶路撒冷

1你們要讚美耶和華!

歌頌我們的上帝,真是美好!

讚美祂,真是快樂合宜!

2耶和華重建耶路撒冷

召集被擄去的以色列人。

3祂醫治心靈破碎的人,

包紮他們的創傷。

4祂決定眾星的數目,

給它們一一命名。

5我們的主偉大無比,充滿力量,

祂的智慧沒有窮盡。

6耶和華扶持謙卑人,

毀滅邪惡人。

7你們要以感恩的心歌頌耶和華,

彈琴讚美我們的上帝。

8祂以雲霞遮蔽天空,

降雨水滋潤大地,

使山上長出綠草。

9祂賜食物給走獸,

餵養嗷嗷待哺的小烏鴉。

10耶和華所喜悅的不是強健的馬匹,

也不是矯捷的戰士,

11而是敬畏祂、仰望祂慈愛的人。

12耶路撒冷啊,要頌讚耶和華;

錫安啊,要讚美你的上帝。

13因為祂使你的城門堅固,

賜福給你的兒女。

14祂使你四境平安,

飽享上好的麥子。

15祂向大地發出命令,

祂的話迅速傳開。

16祂降下羊毛般的白雪,

撒下爐灰般的寒霜。

17祂拋下碎石般的冰雹,

誰能經得住祂降下的嚴寒呢?

18祂一聲令下,冰雪便溶化,

微風便吹拂,河川便奔流。

19祂將自己的話傳於雅各

將自己的律例和法令指示以色列

20祂未曾這樣對待其他國家,

他們不知道祂的律法。

你們要讚美耶和華!