መዝሙር 145 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 145:1-21

መዝሙር 145145 ይህ መዝሙር ተከታታይ በሆኑ የዕብራይስጥ ፊደላት የሚጀምር ሲሆን፣ (ከ13 ጭምር) መነሻዎቹ ወይም መነሻዎቹና መድረሻዎቹ ሆህያት ቍልቍል ሲነበቡ ትርጕም ያላቸውን ቃላት የሚፈጥሩ ናቸው።

ምስጋና ለንጉሡ ለእግዚአብሔር

የዳዊት የምስጋና መዝሙር።

1አምላኬና ንጉሤ ሆይ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤

ስምህን ከዘላለም እስከ ዘላለም እባርካለሁ።

2በየቀኑ እባርክሃለሁ፤

ስምህንም ከዘላለም እስከ ዘላለም አመሰግናለሁ።

3እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤ እጅግ ሊመሰገንም ይገባዋል፤

ታላቅነቱም አይመረመርም።

4ሥራህን አንዱ ትውልድ ለሌላው ትውልድ ያስተጋባል፤

ብርቱ ሥራህን ያውጃል።

5ስለ ግርማህ ውበትና ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ድንቅ ሥራህም145፥5 የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) ስለ ግርማህ ታላቅነትና ክብር፣ ዕፁብ ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ ይላሉ። ያወራሉ።

6ስለ ድንቅ ሥራህ ብርታት ይነጋገራሉ፤

እኔም ስለ ታላቅነትህ ዐውጃለሁ።

7የበጎነትህን ብዛት በደስታ ያወሳሉ፤

ስለ ጽድቅህም በእልልታ ይዘምራሉ።

8እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ርኅሩኅም ነው፤

ለቍጣ የዘገየ፣ ምሕረቱ የበዛ።

9እግዚአብሔር ለሁሉ ቸር ነው፤

ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው።

10እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍጥረትህ ሁሉ ያመሰግንሃል፤

ቅዱሳንህም ይባርኩሃል።

11ስለ መንግሥትህ ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ኀይልህም ይነጋገራሉ፤

12በዚህም ብርቱ ሥራህን፣

የመንግሥትህንም ግርማ ክብር ያስታውቃሉ።

13መንግሥትህ የዘላለም መንግሥት ናት፤

ግዛትህም ለትውልድ ሁሉ ጸንቶ ይኖራል።

እግዚአብሔር ቃሉን ሁሉ ይጠብቃል፤

በሥራውም145፥13 አንድ የማስሬቲክ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) እንዲሁም አብዛኛው የማስሬቲክ ቅጆች የ13 ሁለት ስንኞች የሏቸውም። ሁሉ ቸር ነው።

14እግዚአብሔር የሚንገዳገዱትን ሁሉ ይደግፋል፤

የወደቁትንም ሁሉ ያነሣል።

15የሁሉ ዐይን አንተን በተስፋ ይጠብቃል፤

አንተም ምግባቸውን በወቅቱ ትሰጣቸዋለህ።

16አንተ እጅህን ትዘረጋለህ፤

የሕያዋን ፍጥረታትንም ሁሉ ፍላጎት ታረካለህ።

17እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ፣

በሥራውም ሁሉ ቸር ነው።

18እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፣

በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።

19ለሚፈሩት ፍላጎታቸውን ይፈጽማል፤

ጩኸታቸውን ይሰማል፤ ያድናቸዋልም።

20እግዚአብሔር የሚወድዱትን ሁሉ ይጠብቃል፤

ክፉዎችን ሁሉ ግን ያጠፋል።

21አፌ የእግዚአብሔርን ምስጋና ይናገራል፤

ፍጡር ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ ቅዱስ ስሙን ይባርክ።

New International Version

Psalms 145:1-21

Psalm 145This psalm is an acrostic poem, the verses of which (including verse 13b) begin with the successive letters of the Hebrew alphabet.

A psalm of praise. Of David.

1I will exalt you, my God the King;

I will praise your name for ever and ever.

2Every day I will praise you

and extol your name for ever and ever.

3Great is the Lord and most worthy of praise;

his greatness no one can fathom.

4One generation commends your works to another;

they tell of your mighty acts.

5They speak of the glorious splendor of your majesty—

and I will meditate on your wonderful works.145:5 Dead Sea Scrolls and Syriac (see also Septuagint); Masoretic Text On the glorious splendor of your majesty / and on your wonderful works I will meditate

6They tell of the power of your awesome works—

and I will proclaim your great deeds.

7They celebrate your abundant goodness

and joyfully sing of your righteousness.

8The Lord is gracious and compassionate,

slow to anger and rich in love.

9The Lord is good to all;

he has compassion on all he has made.

10All your works praise you, Lord;

your faithful people extol you.

11They tell of the glory of your kingdom

and speak of your might,

12so that all people may know of your mighty acts

and the glorious splendor of your kingdom.

13Your kingdom is an everlasting kingdom,

and your dominion endures through all generations.

The Lord is trustworthy in all he promises

and faithful in all he does.145:13 One manuscript of the Masoretic Text, Dead Sea Scrolls and Syriac (see also Septuagint); most manuscripts of the Masoretic Text do not have the last two lines of verse 13.

14The Lord upholds all who fall

and lifts up all who are bowed down.

15The eyes of all look to you,

and you give them their food at the proper time.

16You open your hand

and satisfy the desires of every living thing.

17The Lord is righteous in all his ways

and faithful in all he does.

18The Lord is near to all who call on him,

to all who call on him in truth.

19He fulfills the desires of those who fear him;

he hears their cry and saves them.

20The Lord watches over all who love him,

but all the wicked he will destroy.

21My mouth will speak in praise of the Lord.

Let every creature praise his holy name

for ever and ever.