መዝሙር 14
አምላክ የለሽ ሰዎች
14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6
ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።
1ሞኝ14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣
“እግዚአብሔር የለም” ይላል።
ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤
በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።
2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣
እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።
3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤
በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤
አንድ እንኳ፣
መልካም የሚያደርግ የለም።
4የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣
ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣
ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?
5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤
እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።
6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤
እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።
7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!
እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣
ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።
انسان بدكار
1كسی كه فكر میكند خدا نيست، احمق است. چنين شخصی فاسد است و دست به كارهای پليد میزند و هيچ نيكی در او نيست.
2خداوند از آسمان به انسانها نگاه میكند تا شخص فهميدهای بيابد كه طالب خدا باشد. 3ولی همه از او روگردان شدهاند، همه فاسد گشتهاند، در هيچيک از آنها نيكی نيست.
4اين بدكاران بیفهم، خدا را نمیشناسند و قوم مرا مثل نان میبلعند. 5ولی وحشت، آنها را فرا میگيرد زيرا خدا با درستكاران است. 6بلی، وقتی بدكاران اميد آدم بيچاره را نقش بر آب میكنند، خداوند او را در پناه خود میگيرد.
7قوم اسرائيل چقدر شاد خواهند شد وقتی خداوند آنها را رستگار سازد! ای خداوند بيا و قوم خود را نجات ده!