መዝሙር 14 – NASV & NRT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 14:1-7

መዝሙር 14

አምላክ የለሽ ሰዎች

14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሞኝ14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።

2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤

በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤

አንድ እንኳ፣

መልካም የሚያደርግ የለም።

4የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣

ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?

5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤

እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።

6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤

እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።

7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።

New Russian Translation

Псалтирь 14:1-5

Псалом 14

1Псалом Давида.

Господь, кто может пребывать в жилище Твоем?

Кто может жить на святой горе Твоей?

2Тот, чей путь безупречен,

и кто поступает праведно;

кто от чистого сердца истину говорит

3и языком своим не клевещет;

кто не делает ближнему зла

и оскорблений на друга не принимает;

4кто презирает негодяя,

но почитает боящихся Господа;

кто клятву хранит,

пусть даже себе во вред;

5кто дает в долг не ради выгоды

и против невинного взяток не берет.

Поступающий так

никогда не споткнется.