መዝሙር 14 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 14:1-7

መዝሙር 14

አምላክ የለሽ ሰዎች

14፥1-7 ተጓ ምብ – መዝ 53፥1-6

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሞኝ14፥1 በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሞኝ ወይም ተላላ ተብለው የተተረጐሙት የዕብራይስጥ ቃላት ግብረ ገባዊ ንቅዘትን የሚያመለክቱ ናቸው። በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገር የሚሠራ አንድም የለም።

2የሚያስተውል፣ እግዚአብሔርን የሚፈልግ መኖሩን ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ከመንገድ ወጥተዋል፤

በአንድ ላይም ብልሹ ሆነዋል፤

አንድ እንኳ፣

መልካም የሚያደርግ የለም።

4የእግዚአብሔርን ስም የማይጠሩት፣

ሕዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉት፣

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ዕውቀት የላቸውምን?

5ባሉበት ድንጋጤ ውጧቸዋል፤

እግዚአብሔር በጻድቃን መካከል ይገኛልና።

6እናንተ የድኾችን ዕቅድ ለማፋለስ ትሻላችሁ፤

እግዚአብሔር ግን መጠጊያቸው ነው።

7ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።

New International Version – UK

Psalms 14:1-7

Psalm 14

For the director of music. Of David.

1The fool14:1 The Hebrew words rendered fool in Psalms denote one who is morally deficient. says in his heart,

‘There is no God.’

They are corrupt, their deeds are vile;

there is no-one who does good.

2The Lord looks down from heaven

on all mankind

to see if there are any who understand,

any who seek God.

3All have turned away, all have become corrupt;

there is no-one who does good,

not even one.

4Do all these evildoers know nothing?

They devour my people as though eating bread;

they never call on the Lord.

5But there they are, overwhelmed with dread,

for God is present in the company of the righteous.

6You evildoers frustrate the plans of the poor,

but the Lord is their refuge.

7Oh, that salvation for Israel would come out of Zion!

When the Lord restores his people,

let Jacob rejoice and Israel be glad!