መዝሙር 138 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 138:1-8

መዝሙር 138

የምስጋና መዝሙር

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤

በአማልክት ፊት በመዝሙር አወድስሃለሁ።

2ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤

ስለ ምሕረትህና ስለ ታማኝነትህ፣

ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፤

ስምህንና ቃልህን፣

ከሁሉ በላይ ከፍ ከፍ አድርገሃልና።

3በጠራሁህ ቀን መልስ ሰጠኸኝ፤

ነፍሴን በማደፋፈርም ብርቱ አደረግኸኝ።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ የአፍህን ቃል በሰሙ ጊዜ፣

የምድር ነገሥታት ሁሉ ያመስግኑህ።

5የእግዚአብሔር ክብር ታላቅ ነውና፣

ስለ እግዚአብሔር መንገድ ይዘምሩ።

6እግዚአብሔር በከፍታ ስፍራ ቢሆንም፣ ዝቅ ያለውን ይመለከተዋል፤

ትዕቢተኛውን ከሩቅ ያውቀዋል።

7በመከራ መካከል ብሄድም፣

አንተ ሕይወቴን ትጠብቃታለህ፤

በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጅህን ትዘረጋለህ፤

በቀኝ እጅህም ታድነኛለህ።

8እግዚአብሔር በእኔ ላይ ያለውን ዐላማ ይፈጽማል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ለዘላለም ነው።

የእጅህንም ሥራ ቸል አትበል።

King James Version

Psalms 138:1-8

A Psalm of David.

1I will praise thee with my whole heart: before the gods will I sing praise unto thee.

2I will worship toward thy holy temple, and praise thy name for thy lovingkindness and for thy truth: for thou hast magnified thy word above all thy name.

3In the day when I cried thou answeredst me, and strengthenedst me with strength in my soul.

4All the kings of the earth shall praise thee, O LORD, when they hear the words of thy mouth.

5Yea, they shall sing in the ways of the LORD: for great is the glory of the LORD.

6Though the LORD be high, yet hath he respect unto the lowly: but the proud he knoweth afar off.

7Though I walk in the midst of trouble, thou wilt revive me: thou shalt stretch forth thine hand against the wrath of mine enemies, and thy right hand shall save me.

8The LORD will perfect that which concerneth me: thy mercy, O LORD, endureth for ever: forsake not the works of thine own hands.