መዝሙር 132 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 132:1-18

መዝሙር 132

የክብረ በዓል መዝሙር

132፥8-10 ተጓ ምብ – 2ዜና 6፥41-42

መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ዳዊትን፣

የታገሠውንም መከራ ሁሉ ዐስብ፤

2እርሱ ለእግዚአብሔር ማለ፤

ለያዕቆብም ኀያል አምላክ እንዲህ ሲል ተሳለ፤

3“ወደ ቤቴ አልገባም፤

ዐልጋዬም ላይ አልወጣም፤

4ለዐይኖቼ እንቅልፍን፣

ለሽፋሽፍቶቼም ሸለብታ አልሰጥም፤

5ለእግዚአብሔር ስፍራን፣

ለያዕቆብም ኀያል አምላክ ማደሪያን እስካገኝ ድረስ።”

6እነሆ፤ በኤፍራታ ሰማነው፤

በቂርያትይዓሪም132፥6 አንዳንዶቹ ያዓር ይላሉ። አገኘነው።

7“ወደ ማደሪያው እንግባ፤

እግሮቹ በሚቆሙበት ቦታ እንስገድ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ተነሥ፤

አንተና የኀይልህ ታቦት ወደ ማረፊያህ ስፍራ ሂዱ።

9ካህናትህ ጽድቅን ይልበሱ፤

ቅዱሳንህም እልል ይበሉ።”

10ስለ አገልጋይህ ስለ ዳዊት ስትል፣

የቀባኸውን ሰው አትተወው።

11እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ፤

በማይታጠፍም ቃሉ እንዲህ አለ፤

“ከገዛ ራስህ ፍሬ፣

በዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ።

12ወንዶች ልጆችህ ኪዳኔን፣

የማስተምራቸውንም ምስክርነቴን ቢጠብቁ፣

ልጆቻቸው በዙፋንህ ላይ፣

ለዘላለም ይቀመጣሉ።”

13እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፣

ማደሪያውም ትሆን ዘንድ ወድዷልና እንዲህ አለ፤

14“ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤

ፈልጌአታለሁና በእርሷ እኖራለሁ።

15እጅግ አትረፍርፌ እባርካታለሁ፤

ድኾቿን እንጀራ አጠግባለሁ።

16ለካህናቷ ድነትን አለብሳለሁ፤

ቅዱሳኗም በደስታ ይዘምራሉ።

17“በዚህም ለዳዊት ቀንድ132፥17 እዚህ ላይ ቀንድ የጥንካሬ ትእምርት ሲሆን፣ ንጉሥን ያመለክታል። አበቅላለሁ፤

ለቀባሁትም ሰው መብራት አዘጋጃለሁ።

18ጠላቶቹን ኀፍረት አከናንባቸዋለሁ፤

እርሱ ግን በራሱ ላይ የደፋው ዘውድ ያበራል።”

New International Version – UK

Psalms 132:1-18

Psalm 132

A song of ascents.

1Lord, remember David

and all his self-denial.

2He swore an oath to the Lord,

he made a vow to the Mighty One of Jacob:

3‘I will not enter my house

or go to my bed,

4I will allow no sleep to my eyes

or slumber to my eyelids,

5till I find a place for the Lord,

a dwelling for the Mighty One of Jacob.’

6We heard it in Ephrathah,

we came upon it in the fields of Jaar:132:6 Or heard of it in Ephrathah, / we found it in the fields of Jearim. (See 1 Chron. 13:5,6) (and no quotation marks around verses 7-9)

7‘Let us go to his dwelling-place,

let us worship at his footstool, saying,

8“Arise, Lord, and come to your resting-place,

you and the ark of your might.

9May your priests be clothed with your righteousness;

may your faithful people sing for joy.” ’

10For the sake of your servant David,

do not reject your anointed one.

11The Lord swore an oath to David,

a sure oath he will not revoke:

‘One of your own descendants

I will place on your throne.

12If your sons keep my covenant

and the statutes I teach them,

then their sons shall sit

on your throne for ever and ever.’

13For the Lord has chosen Zion,

he has desired it for his dwelling, saying,

14‘This is my resting-place for ever and ever;

here I will sit enthroned, for I have desired it.

15I will bless her with abundant provisions;

her poor I will satisfy with food.

16I will clothe her priests with salvation,

and her faithful people shall ever sing for joy.

17‘Here I will make a horn132:17 Horn here symbolises strong one, that is, king. grow for David

and set up a lamp for my anointed one.

18I will clothe his enemies with shame,

but his head shall be adorned with a radiant crown.’