መዝሙር 131 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 131:1-3

መዝሙር 131

በእግዚአብሔር መታመን

የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ልቤ አልታበየም፤

ዐይኔ ከፍ ከፍ አላለም፤

ሐሳቤ ለዐጕል ትልቅነት አልተነሣሣም፤

ከዐቅሜም በላይ አልተንጠራራሁም።

2ነገር ግን ነፍሴን ጸጥ፣ ዝም አሰኘኋት፤

ጡት የጣለ ልጅ ዐርፎ እናቱ ላይ እንደሚቀመጥ፣

ነፍሴ ጡት እንዳስተዉት ሕፃን በውስጤ ጸጥ አለች።

3እስራኤል ሆይ፤ ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣

በእግዚአብሔር ተስፋ አድርግ።

King James Version

Psalms 131:1-3

A Song of degrees of David.

1LORD, my heart is not haughty, nor mine eyes lofty: neither do I exercise myself in great matters, or in things too high for me.131.1 exercise…: Heb. walk131.1 high: Heb. wonderful

2Surely I have behaved and quieted myself, as a child that is weaned of his mother: my soul is even as a weaned child.131.2 myself: Heb. my soul

3Let Israel hope in the LORD from henceforth and for ever.131.3 henceforth: Heb. now