መዝሙር 125 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 125:1-5

መዝሙር 125

እግዚአብሔር የሚታመኑበትን ይጠብቃል

መዝሙረ መዓርግ።

1በእግዚአብሔር የሚታመኑ፣

ሳትናወጥ ለዘላለም እንደምትኖር እንደ ጽዮን ተራራ ናቸው።

2ተራሮች ኢየሩሳሌምን እንደ ከበቧት፣

ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም፣ እግዚአብሔር በሕዝቡ ዙሪያ ነው።

3ጻድቃን እጃቸውን ለክፋት እንዳያነሡ፣

የክፉዎች በትረ መንግሥት፣

ለጻድቃን በተመደበች ምድር ላይ አያርፍም።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ መልካም ለሆኑ፣

ልባቸውም ለቀና መልካም አድርግ።

5ወደ ጠማማ መንገዳቸው የሚመለሱትን ግን፣

እግዚአብሔር ከክፉ አድራጊዎች ጋር ያስወግዳቸዋል።

በእስራኤል ላይ ሰላም ይውረድ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 125:1-5

125

1主を信頼する人は、シオンの山のように、

どのような状況でも動じません。

2エルサレムがその周囲の山々に守られているように、

主もご自分の民を取り囲んで、守ってくださいます。

3神を信じて従っている人々を悪者どもが支配し、

悪事を押しつけるようなことが

あってはならないからです。

4ああ主よ、心のまっすぐな

正しい人々を恵んでください。

5そして、悪者どもは、処刑場へ連れ去ってください。

イスラエルに平和がありますように。